በደራሲ ደሳለኝ ስዩም የተፃፈው “የታሰረ ፍትህ” የተሰኘ ኢ-ልብወለድ መጽሐፍ ታትሞ ለገበያ ቀረበ፡፡ የመጽሐፉ ጭብጥ በህዝብና በገዢው ፓርቲ ዙሪያ የሚያጠነጥን ነው ተብሏል፡፡ በ3 ምዕራፎችና በ148 ገፆች የተዘጋጀው መጽሐፉ፤ በ35 ብር ከ50 እየተሸጠ ነው፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “ደም የተፋ ብዕር” የሚል የግጥም መድበልና “የጠረፍ ህልሞች” የተሰኘ ረዥም ልብወለድ ለአንባቢያን ማድረሱ ይታወቃል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና