Saturday, 07 June 2014 14:22

የማይታመን የፍቺ ክፍያ - 4.8 ቢ. ዶላር!

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ሩሲያዊው ቢሊየነር ድሚትሪ ራይቦሎቭሌቭ፤ በቅርቡ ከቀድሞ ሚስቱ ጋር የፈፀመውን ፍቺ እንደ ድንገተኛ የቢዝነስ ኪሳራ መቁጠሩ አይቀርም። የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብን እኮ ነው ክፈላት የተባለው፡፡ ቢሊዬነሩ 27 ዓመት በትዳር አብራው ከዘለቀችው ኢሌና ጋር ፍቺ መፈፀሙን ተከትሎ የስዊስ ፍ/ቤት የቀድሞ ባለቤቱ 4.8ቢ. ዶላር ብት ልትካፈል ይገባል ሲል ወስኗል፡፡ የኢሌና ጠበቃ በሰጠው መግለጫ “እጅግ ውድ ፍቺ ነው” ብሎታል። ይሄ እጅግ ውድ የፍቺ ክፍያ ለድሚትሪ ከፍተኛ ኪሳራ ሲሆን ለቀድሞ ሚስቱ ግን የማይታመን የሃብት ጎርፍ ነው፡፡
የዛሬ 15 ዓመት ደግሞ ሌላ ውድ ፍቺ ተፈጽሟል። አውስትራሊያዊው የሚዲያ ከበርቴና ለ32 ዓመታት በትዳር አብራው የኖረችው የ3 ልጆቹ እናት አና ሙድሮክ፤ እ.ኤ.አ በ1999 ዓ.ም ፍቺ ሲፈጽሙ ፍ/ቤት ለሚስትየው የ1.7 ቢሊዮን ዶላር ሃብት (110 ሚ.ዶላር ካሽ ይጨምራል) እንድትካፈል ነበር የወሰነላት። ከሃብት ክፍፍሉም በኋላ ሁለቱም የየራሳቸውን ህይወት ቀጥለዋል፡፡ በእርግጥ ሩፐርት ሙድሮክ በ38 ዓመት ከምታንሰው ዌንዲ ዴንግ ጋር ትዳር የመሰረተው ፍቺ በፈፀመ በ17ኛ ቀኑ ነበር ሳይፈታ በፊት ያዘጋጀ እኮ ነው የሚመስለው፡፡ አናም በበኩሏ፤ ከወራት ቆይታ በኋላ አንድ ኢንቨስተር አግብታለች፡፡ በሃብት ላይ ሃብት አትሉም፡፡ እነ አሜሪካን በመሳሰሉ የበለፀጉ አገራት፤ ቢሊዬነሮችን አግብቶ መፍታት አትራፊ ኢንቨስትመንት እየሆነ ነው፡፡

Read 1382 times