Print this page
Saturday, 07 June 2014 14:28

ፌስቡክ - ሰው አልባ አውሮፕላን

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ዋነኛ ስራው - የኢንተርኔት አገልግሎት
በአመት ወደ 8 ቢ. ዶላር ገደማ የአገልግሎት ሽያጭ ያገኛል
ባለፈው አመት 1.5 ቢ. ዶላር አትርፏል
የኩባንያው ሃብት 18 ቢ. ዶላር ገደማ ይገመታል
በኢንተርኔት አለም በ2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል - 1.3 ቢ. ገደማ ደንበኞችን በማስተናገድ
በደንበኞች ብዛት አቻ ያልተገኘለት ፌስቡክ፣ ገና የረካ አይመስልም። ተጨማሪ ደንበኞችን ለማፍራት ዘዴ ማፈላለግ ከጀመረ ውሎ አድሯል። ከከተማ ርቀው የሚገኙና በቀርፋፋ የኢንተርኔት ግንኙነት የተቸገሩ ብዙ ሚሊዮን ሰዎች አሉ።
እነዚህን ሁሉ ደንበኛ ለማድረግ አዲስ ብልሃት ያስፈልጋል። በየአገሩ እየሄደ የግንኙት መስመር መዘርጋት አይችልም። እንደኢትዮጵያ በመሳሰሉ አገራትማ፣ ከመንግስት ውጭ የቴሌኮም አገልግሎት መስጠት ክልክል ነው።
ፌስቡክ የወጠነው ዘዴ፣ ከሰማይ ላይ የኢንተርኔት አገልግሎት ማቅረብ ነው። ከምድር በ30 ኪሎሜትር ርቀት የሚያንዣብቡ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ለማሰማራት ሙከራ እያከናወነ የሚገኘው ፌስቡክ፤ በፀሐይ ሃይል ለረዥም ጊዜ አየር ላይ የሚቆዩ አውሮፕላኖችን ሰርቷል።
ከሰማይ ላይ የኢንተርኔት አገልግሎት ለማቅረብ እየሞከረ ያለው ፌስቡክ ብቻ አይደለም። ጉጉልም በፊናው እየተጣጣረ ነው።
በአንድ በኩል በከፍተኛ ርቀት የሚንሳፈፉ “ባሉኖች”ን ለመጠቀም ራሱን የቻለ ፕሮጀክት ሲያከናውን የቆየው ጉጉል፤ በፀሃይ ሐይል ለ5 ዓመታት አየር ላይ የሚያንዣብቡ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ሰርቷል።

Read 3096 times
Administrator

Latest from Administrator