Print this page
Saturday, 28 June 2014 11:16

ህፃናት ለእግዚአብሔር የፃፏቸው ደብዳቤዎች

Written by 
Rate this item
(18 votes)

ውድ እግዚአብሔር፡-
ትልቋ እማማ ወደ ቤቷ ስትሄድ ከእኛ ጋር የምትሆን ሌላ እማማ ልትልክልኝ ትችላለህ?
ሶፊ - የ4 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
አባቢ ዶክተር እንድሆን ይፈልጋል፡፡ እኔ ደሞ አልፈልግም፡፡ አንተ ግን ሳይንቲስት እንድሆን ትፈቅድልኝ የለ?
ብሩክ - የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ዳዲን ካየሁት ብዙ ጊዜ ሆኖኛል፡፡ ማሚን ስጠይቃት የሄደበትን አታውቀውም፡፡ አንተ ጋ መጥቷል እንዴ?
ጆሲ - የ5 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
በዚህ ዓመት ከክፍላችን አንደኛ የሚወጣው ማነው? ለእኔ ብቻ በጆሮዬ ንገረኝ፡፡
ሄለን - የ5 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ታላቅ እህቴ፤ ማሚ ያስቀመጠችውን ቸኮላት ሰርቃ ስትበላ አየኋት፡፡ ለማሚ ልንገርባት ወይስ አንተ ትቆጣታለህ?
ዴቭ - የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
አንተ ጋ ትምህርት ቤት የለም አይደል! አለ እንዴ?
ሳሚ - የ7 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ከክፍላችን ልጆች ሁሉ ቀድሜ መሮጥ እንድችል ታደርገኛለህ? እርግጠኛ ነኝ ትችላለህ፡፡
ፊሊፕ - የ5 ዓመት ህፃን

Read 3638 times
Administrator

Latest from Administrator