ላለ - መጨቆን
ሞት ይቅር ይላሉ…
ሞት ቢቀር አልወድም
ከድንጋይ ---ቋጥኙ---
ከሰው ፊት አይከብድም፡፡
ማጣት ክፉ ክፉ፤
ችግር ክፉ ክፉ፤
ተብሎ ይወራል
ከባርነት ቀንበር
ከሬት መች ይመራል፡፡
***
ለ- ጅገና
ተው! ተመለስ በሉት
ተው! ተመለስ በሉት!
ያንን መጥፎ በሬ
ከጠመደ አይፈታም ያገሬ ገበሬ
* * *
ያባቴ ነው ብሎ፤
የናቴ ነው ብሎ፤
ይፋጃል በርበሬ
አባት የሌለው ልጅ፤
እናት የሌለው ልጅ፤
አይሆንም ወይ አውሬ
ለወንድ - አደር
ዓይንሽ የብር ዋጋ
ጥርስሽ የብር ዋጋ
ወዳጆችሽ በዙ ከስንቱ ልዋጋ?
(ከክፍሌ አቦቸር (ሻምበል)
“አንድ ቀን” የግጥም መድበል፤ 1982፣ የተወሰዱ)
Published in
የግጥም ጥግ