Saturday, 19 July 2014 12:50

“የእኛ ሰው ገመና” መፅሀፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

“የአዲስ አበባ ጉዶች” እና “ኢትዮጵያን ማን ይታደጋት” በሚሉት መፅሀፎቹ የሚታወቀው ጋዜጠኛና ደራሲ አቤል አለማየሁ፤ “የእኛ ሰው ገመና” የተሰኘውን ሦስተኛ መፅሀፉን በሳምንቱ መገባደጃ ላይ ለንባብ አብቅቷል፡፡ የተደበቁ እውነቶችን ምፀታዊ ወጎች፣ ማህበራዊና ወሲባዊ ጉዳዮችን የሚዳስሰው መፅሀፉ፤ በተለይም በድንግልና ንግድ፣ በሴት ሰዶማውያውን፣ በልቅ ወሲብና በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵዊያንን አስገራሚ ገመናዎች በስፋት ያስቃኛል፡፡ ለአፍሪካ ዋንጫ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዞ የነበረው አቤል፤ በቆይታው የታዘባቸውን የሀበሻ ልጆች ገመና ዋና የመፅሃፉ ትኩረት ማድረጉን ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡
በ208 ገፆች የተቀነበበውና በርካታ ማህበራዊ ርዕሰ ጉዳዮችን የሚዳስሰው መፅሀፉ፤ በ49 ብር ከ65 ሳንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 3391 times