በገጣሚ ትዕግስት ማሞ የተሰናዳው “የእምነት ወጎች” የተሰኘ የግጥም ስብስብ በሲዲ ተዘጋጅቶ ለገበያ የቀረበ ሲሆን ባለፈው ረቡዕ ምሽት በዋቢ ሸበሌ ሆቴል በድምቀት ተመርቋል፡፡
16 ግጥሞችን ያካተተው የግጥም ሲዲ በተመረቀበት ወቅት የቀድሞ መምህሯ ረዳት ፕ/ር ሙሉጌታ ጀዋሬ፣ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራና ሌሎች ገጣሚያንም ስራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡ በእለቱ ገጣሚ ትዕግስት ስራዎቿን ያቀረበች ሲሆን የታዳሚያን መግቢያ አንድ ሲዲ ነበር፡፡
በሲዲው ውስጥ ከተካተቱት 16 ግጥሞች መካከል “ትዝታና ፍቅር”፣ “ጋዜጠኛው”፣ “ይድረስ ለወንድሜ”፣ “ይማርሽ”፣ “አድዋ”፣ “ክፈለኝ” እና የሲዲው መጠሪያ የሆነው “የእምነት ወጎች” የሚገኙበት ሲሆን በግጥሞቹ ውስጥ ማህበራዊ ጉዳዮች በምፀትና በትዝብት ተዳስሰዋል፡፡ በ50 ብር እየተሸጠ ያለው የግጥም ሲዲው በአሁኑ ሰዓት ከጎጃም በረንዳ ወደ ዮሃንስ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው “ግሬስ” ህንፃ ላይ እየተከፋፈለ ይገኛል፡፡
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል