Saturday, 16 August 2014 11:06

“የአእምሮ ጉዳይ” መፅሀፍ ገበያ ላይ ዋለ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

በደራሲ ወንድሙ ነጋሽ የተፃፈው “የአዕምሮ ጉዳይ” የተሰኘ መፅሃፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ አዕምሯችን የማናውቀው ፕላኔት ነው የሚለው መፅሃፉ፤ ስለ አእምሮ ህመምና ማህበረሰቡ ለአእምሮ ህመምተኞች ስላለው አመለካከት፣ ለአዕምሮ መታወክ መንስኤ ስለሚሆኑ ጉዳዮችና መፍትሄዎቻቸው… የሚዳሰስስ ነው፡፡ በ192 ገፆች የተቀነበበው መፅሀፉ፤ በ39 ብር ከ60  ለገበያ የቀረበ ሲሆን የመፅሀፉ ሽያጭ ገቢ በአዕምሮ ህመም ለሚሰቃዩ ወገኖች ለሚቋቋመው ድርጅት መርጃ ይሆናል ተብሏል፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “የአዕምሮ አስተዳደር ሞዴል” እና “ፍቅር ምንድን ነው” የሚሉ መፃህፍትን ለአንባቢያን ማድረሳቸው ይታወቃል፡፡

Read 2505 times