በአገራችን የሚከበሩ መንፈሳዊና ብሄራዊ ፌስቲቪሎችን የሚያስቃኝ “የኢትዮጵያ ፌስቲቫል ማውጫ” የተሰኘ መፅሀፍ ሰሞኑን ታትሞ የወጣ ሲሆን በነፃ እንደሚሰራጭ ታውቋል፡፡ መፅሀፉ ከ15 በላይ የመስቀል በዓል አከባበሮች፣ በተለያዩ አምስት አካባቢዎች የሚካሄዱ የጥምቀት በዓላት፣ የገና፣ የመውሊድ እና የአረፋ እንዲሁም የአሸንዳ፣ የእሬቻና ፍቼ በዓላትን ጨምሮ በርካታ ፌስቲቫሎችን ያካተተ ሲሆን፤ በዓላቱ መቼና እንዴት እንዲሁም ለምን እንደሚከበሩ መረጃ ይሰጣል፡፡ ማውጫው ለሀገር ውስጥ ጎብኚዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ለመገናኛ ብዙሃንና ለአስጎብኚዎች በነፃ ይሰራጫል ተብሏል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና