Saturday, 23 August 2014 11:12

ኮካኮላ 50ሺ ሰዎች ተጠቃሚ የሚያደርግ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ይፋ አደረገ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የኮካኮላ ፋውንዴሽንና ወርልድ ቪዥን ሪፕሌኒሽ አፍሪካ ኢኒሼቲቭ በተባለው
ፕሮጀክት አማካኝነት በትግራይ ክልል የህብረተሰቡን የጤና ሁኔታ ለማሻሻልና የማያቋርጥ ንፁህ ውሃ ለማቅረብ ያስችላል ያለውን የ19 ማሊዮን ብር ፕሮጀክት ይፋ አደረገ፡፡
ፕሮጀክቱ የአፍሪካ ኢኒሼቲቭ ሶስተኛው ፕሮጀክት ሲሆን ኢንሼቲቩ በኢትዮጵያ ላለፉት ሶስት አመታት ተመሳሳይ ፕሮጀክቶችን ነድፎ በአማራ፣ በደቡብ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በሚገኙ ሰባት የገጠር ወረዳዎች 28 ሚሊዮን ብር በማውጣት ማከናወኑን በትናንትናው እለት ኩባንያው በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡ በዚህም ለ73,400 ዜጐች ንፁህ የመጠጥ ውሃ ማቅረብ መቻሉ ተመልክቷል፡፡
ፕሮጀክቱ ኮካኮላ ኩባንያ እስከ 2007 ዓ.ም ድረስ ለ2 ማሊዮን አፍሪካውያን ንፁህ የመጠጥ ውሃ ለማቅረብ የገባው ቃል አካል መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በትግራይ የሚተገረው ፕሮጀክት 50 ሺህ ሰዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሏል፡፡

Read 1249 times