Saturday, 23 August 2014 11:58

የጳውሎስ ኞኞ የህይወት ታሪክ ዛሬ ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(4 votes)

በጋዜጠኛ ደረጀ ትዕዛዙ የተጻፈው የዕውቁ ጋዜጠኛ፣ ደራሲና የታሪክ ጸሐፊ ጳውሎስ ኞኞ የህይወት ታሪክን የያዘው “ጳውሎስ ኞኞ ከ1926-1984” የተሰኘ መፅሐፍ ዛሬ ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አዲሱ ህንጻ፣ 6ኛ ፎቅ ላይ ይመረቃል፡፡ በስነ-ስርዓቱ ላይ የጳውሎስ ኞኞ ቤተሰቦች፣ አድናቂዎች፣ ጋዜጠኞችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡

Read 2753 times