Saturday, 13 September 2014 13:40

“የክረምት ፊደላት” የኪነ-ጥበብ ዝግጅት ለ3ኛ ጊዜ ተካሄደ

Written by  መንግሥቱ አበበ
Rate this item
(0 votes)

እናት ማስታወቂያ እና አጋ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ከጀርመን የባህል ማእከል፣ ከሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያና ከካፒታል ሆቴልና ስፓ ጋር በመተባበር “የክረምት ፊደላት” የተሰኘ የኪነ-ጥበብ ዝግጅት ለ3ኛ ጊዜ ባለፈው ማክሰኞ ማቅረባቸው ተገለፀ፡፡
በካፒታል ሆቴልና ስፓ በተካሄደው የኪነ-ጥበብ ምሽት ፕሮግራም ላይ ገጣሚ ሰለሞን ሳህለ፣ ምህረት ከበደ፣ ይታገሱ ጌትነት፣ ዮሐንስ ኃ/ማርያም፣ መስፍን ወ/ትንሳይ እና ፍሬዘር አድማሱ የግጥም ስራቸውን አቅርበዋል፡፡
ገጣምያኑ በጋራ በመሆንም ከነባሩ የቡሄና እና የአበባየሆሽ ጨዋታ ስንኞችን በመምዘዝ ለየት ያሉ የፈጠራ ግጥሞችን በቅብብሎሽ አቅርበዋል፡፡
“የክረምት ፊደላት” የኪነ-ጥበብ ዝግጅት በየአመቱ በክረምት ወቅት የሚካሄድ ሲሆን የሰሞኑ ለ3ኛ ጊዜ የተዘጋጀ መሆኑን የጠቆሙት የፕሮግራሙ አዘጋጆች፤ ከዚህም በተጨማሪ “የበጋ ፊደላት”፣ “የፀደይ ፊደላት”፣ እና “የመኸር ፊደላት” በሚል ስያሜ ወቅቱን ጠብቀው የጥበብ ዝግጅቶችን እንደሚያሰናዱ አስታውቀዋል፡፡

Read 1324 times