Saturday, 20 September 2014 10:22

የአዳም ረታ “መረቅ” በገበያ ላይ ሊውል ነው

Written by 
Rate this item
(3 votes)

        በአንጋፋው ደራሲ አዳም ረታ የተጻፈው “መረቅ” የተሰኘ የረጅም ልቦለድ መጽሃፍ ሰሞኑን በገበያ ላይ ይውላል፡፡ ለደራሲው ስምንተኛው የሆነው ይሄው መፅሃፍ፤ ከስድስት መቶ በላይ ገጾች ያሉት ሲሆን፣ በቅርቡ በተለያዩ መጽሃፍት መደብሮችና አዟሪዎች ለገበያ እንደሚውል ታውቋል፡፡ ደራሲ አዳም ረታ ከዚህ በፊት “ማህሌት”፣ “ግራጫ ቃጭሎች”፣ “እቴሜቴ ሎሚ ሽታ”፣ “አለንጋ እና ምስር”፣ “ከሰማይ የወረደ ፍርፍር”፣ “ህማማት እና በገና” እና “ይወስዳል መንገድ፣ ያመጣል መንገድ” የተሰኙ ተወዳጅ የአጫጭርና የረጅም ልቦለድ መጽሃፍትን ለንባብ አብቅቷል፡፡ አዳም ከዚህ በተጨማሪም፣ በአይነቱ ለየት ያለና ከ1ሺህ 600 በላይ ገጾች እንደሚኖረው የተነገረለትን፣ “የስንብት ቀለማት” የተሰኘ ረጅም ልቦለዱን እያጠናቀቀ እንደሚገኝ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ለረጅም አመታት ኑሮውን በባህር ማዶ ያደረገው አዳም ረታ፣ ሰሞኑን ወደ አዲስ አበባ እንደመጣ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 2948 times