Monday, 22 September 2014 13:47

‹‹...ጽንስ ማቋረጥ ስለፈለገች ብቻም ጽንስ አይቋረጥም...››

Written by  ፀሐይ ተፈረደኝ ከኢሶግ
Rate this item
(12 votes)

በአለም አቀፍ ደረጃ በየአመቱ ወደ 20 ሚሊዮን የሚሆኑ ደህንነቱ ያልተጠበቀ ጽንስ ማቋረጥ ሲፈጸም ይህም
ከ10/እርግዝናዎች አንድ ደህንነቱ ያልተጠበቀ እርግዝና እንደሚከወን ያሳያል፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ ከሚያጋጥሙት ጽንስ ማቋረጦች 1/3ኛ የሚሆኑት ደህንነቱ ያልተጠበቀ ነው፡፡
90 % የሚሆነው ደህንነቱ ያልተጠበቀ ጽንስ ማቋረጥ የሚፈጸመው በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት ነው፡፡
ደህንነቱ ያልተጠበቀ ጽንስ ማቋረጥ በአለም አቀፍ ደረጃ ከ70-200 ሺህ ለሚሆኑ እናቶች ሞት
ምክንያት ነው፡፡
..ምንጭ (WHO, Alan Guttmacher Institute, and Family Health International)
ከላይ የጠጠቀሱት ምንጮች ጨምረው እንደገለጹት ለበርካታ ዘመናት ማለትም እስከ 1800ዎቹ ድረስ ጽንስን
ማቋረጥ በአለም አቀፍ ደረጃ በተለያዩ መንገዶች ይካሄድ ነበር፡፡ ነገር ግን በሁሉም ቦታዎች የሚካሄደው
በህገወጥ መንገድ ነበር፡፡ የባህል ሕክምና የሚያደርጉ ሰዎች እራሳቸው ድርጊቱን ከመፈጸማቸው ባሻገር ሌሎች
ሰዎችንም እያሰለጠኑ እርስ በእርሳቸው እንዲረዳዱ ያደርጉ ነበር፡፡ ነገር ግን በህገ ወጥ ጽንስ ማቋረጥ ምክንያት
ለህልፈት የሚዳረጉት ሴቶች ቁጥር እያደገ በመምጣቱ አለምአቀፉ ህብረተሰብ ድርጊቱ በህግ የታገዘ እንዲሆንና
በዚያም መሰረት ሆስፒታሎች እና የጤና ተቋማት የሴቶቹን ደህንነት በጠበቀ መልኩ ጥንቃቄ የተሞላበት እና
ደህንነቱ የተጠበቀ ጽንስን ማቋረጥ እንዲፈጽሙ ህግ እንዲወጣ ምክንያት ሆኖአል፡፡ ስለሆነም ብሪ..ይን በ1803
ዓ/ም ለመጀመሪያ ጊዜ ህጉን አወጣች፡፡ ከዚያ በሀዋላ በአለም ላይ የተለያዩ ሐገራት በየደረጃው ጥንቃቄ የጎደለው
ጽንስን ማቋረጥ ተግባር እንዲወገድ ህግ አውጥተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት የወንጀለኛ መቅጫ ሕጉን ሲያሻሽል ከሰኔ 1/97 ጀምሮ በስራ ላይ የሚውል
የወንጀል ሕግ በአዋጅ ቁጥር 414/96 አውጥቶአል፡፡ ተሸሽሎ የወጣው ሕግ ካካተታ ቸው ጉዳዮች መካከል
ጽንስ ማቋረጥን የሚመለከት ይገኝበታል፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስ..ርም በዚህ ሕግ መሰረት የአሰራር መመሪያውን
ቀርጾ ከሰኔ 1998 ዓ/ም ጀምሮ በተግባር ላይ እንዲውል አድርጎአል፡፡
ቁ.3. የወንጀል ሕጉ ድንጋጌ ፣
በአንቀጽ 551 መሰረት .. ፅንስን ማቋረጥ በህግ የተፈቀደባቸው ሁኔታዎች..
1. በሕክምና ሙያ በተፈቀደ የጊዜ ገደብ ውስጥ በህክምና ተቋም ጽንስ ሲቋረጥ በወንጀል
የማያስቀጣው፣
ሀ. በመደፈር ወይንም በዘመድ መካከል በተደረገ የግብረስጋ ግንኙነት ምክንያት ጽንሱ የተገኘ ሲሆን፣
ለ. የእርግዝናው መቀጠል በእናቲቱም ሆነ በፅንሱ ሕይወት ወይንም በእናቲቱም ጤንነት ላይ አደጋ
የሚያስከትል ሲሆን ወይንም የልጁ መወለድ በእናቲቱ ጤንነት ወይንም ሕይወት ላይ አደጋ የሚያመጣ ሲሆን፣
ሐ. ጽንሱ ሊድን የማይችል ከባድ የአካል ጉድለት ያለው (ዲፎርምድ) ሲሆን ወይም
መ. አንዲት እርጉዝ ሲት የአካል ወይንም የአእምሮ ጉድለት ያለባት በመሆንዋ ወይም ለአካለ መጠን ያልደረሰች
በመሆንዋ የሚወለደውን ህጻን ለማሳደግ የህሊናም ሆነ የአካል ዝግጅት የሌላት ሲሆን ነው፡፡
የኢፊድሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሰኔ 1998 አዲስ አበባ
እንደውጭው አቆጣጠር በ2003 ዓ/ም ጤና ጥበቃ ያወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው በኢትዮጵያ አንድ
ሶስተኛው የእናቶች ሞት ምክንያት በህገወጥ መንገድ ጽንስን ማቋረጥ ነው፡፡ በኢትዮጵያ በአመት ወደ 22 ሺህ
እናቶች ከወሊድ ጋር በተያያዘ ሁኔታ የሚሞቱ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ እድሜያቸው ከአስራ አምስት አመት እስከ
አርባ ዘጠኝ አመት የሚገመቱ ስምንት ሺሕ ያህል እናቶች በህገወጥ ውርጃ ምክንያት ለህልፈት እንደሚዳረጉ
ተረጋግጦአል፡፡ በእርግጥ በትክክል ተጠቃሽ ሊሆኑ የሚችሉ ጥናቶች ባይኖሩም ከየሆስፒታሉ ከሚሰሙ ሪፖርቶች
እንዲሁም አልጋ ከያዙ ህመምተኞች ሁኔታ ከሚገኙ መረጃዎች በመነሳት ህገወጥ ውርጃ ድርጊቱ በመጠኑ እየቀነሰ
ሄዶአል ማለት ያስችላል፡፡ ለህገወጥ ውርጃው መቀነስ እንደ አንድ ዋነኛ ምክንያት የሚጠቀሰው ህጉ ላይ መሻሻል
መደረጉ ነው፡፡
ዶ/ር ሰሎሞን ቁምቢ /በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተባባሪ ፕሮፌሰር/
በዚህ እትም ለንባብ ያቀረብነው ጽንስን በማቋረጥ ተግባር ላይ የሚያተኩረው ሕግም ሆነ መመሪያው ከወጣ
ጀምሮ በህብረተሰቡ ዘንድ ያለው አጠቃቀም እና በሕክምና ተቋማቱ ዘንድ ያለው አሰራር ምን ይመስላል?
የሚለውን በሚመለከት ይሆናል፡፡ በምንጭነት የምናቀርባቸው ባለሙያዎች ዶ/ር ደመቀ ደስታ በአይፓስ
ኢትዮጵያ ሲኒየር አድቫይዘር ፣ዶ/ር ጌትነት በቀለ በርጌስ ክሊኒክ ባለቤትና የህክምና ባለሙያ ከተክለሀይማኖት
ጠቅላላ ሆስፒታል ሲ/ር ነጻነት አባተ እና ከበርጌስ ክሊኒክ ሲ/ር አበባ ስለሺ ናቸው፡፡
እንደ ዶ/ር ደመቀ አገላለጽ ኢትዮጵያ በአለም በተለይም ከሰሃራ በታች ባሉ ሀገራት ብዙ እናቶች
ይሞቱባታል ተብለው ከሚጠቀሱት አገራት መካከል ናት፡፡ 100.000/ አንድ መቶ ሺህ/ ከሚሆኑ በህይወት
ከሚወለዱ ሕጻናት ወደ 673/ የሚሆኑ እናቶች ባጠቃላይ ከእርግዝና ጋር በተያያዘ ሕይወታቸውን ያጡ የነበረ
ሲሆን ለሞት ምክንያት ከሚሆኑት ውስጥ አንዱ ደህንነቱ ያልተጠበቀ ጽንስን ማቋረጥ ነበር፡፡ ደህንነቱን
ያልጠበቀ ጽንስ ማቋረጥ 32 ኀ ለሚሆነው የእናቶች ሞት ምክንያት ነበር፡፡
ዶ/ር ጌትነት በቀለ የበርጌስ ክሊኒክ ባለቤትና የህክምና ባለሙያ እንደሚሉት
‹‹....በአብዛኛው ደህንነቱ የተጠበቀ ጽንስን ማቋረጥ የህክምና አገልግሎት የምንሰጠው እስከ 12/ ሳምንት ወይንም
ሶስት ወር ድረስ ያለውን እርግዝና ነው፡፡ ይህንንም ደህንነቱ የተጠበቀ ጽንስ የማቋረጥ አገልግሎት ሕጉ
በሚፈቅደው መሰረት ልምድ ባላቸው የህክምና ባለሙያዎች አማካኝነት በተሟላ መልኩ እንሰጣለን፡፡
ይህንን አገልግሎት በሚመለከት ካለፉት ጊዜያት ጋር ሲነጻጸር ብዙ ልዩነቶች ይታዩበታል፡፡ አይፓስ እና
ሜሪስቶፕስ ለህክምና ባለሙያዎቹ ከሚሰጡት ስልጠና ባሻገርም አገልግሎቱን የምን ሰጥበትን ቁሳቁስ የሚረዱን
በመሆኑ ብዙ የተሻሻለ ነገር አለ፡፡ዛሬ ደህንነቱ የተጠበቀ ጽንስ ማቋረጥን በሚመለከት ከየትኛው ሆስፒታል
ወይንም ክሊኒክ ልሂድ ብሎ መጨነቅ አይገባም፡፡ ስልጠናው በሁሉም ቦታ እየተሰጠ ስለሆነ በተለይም በአዲስ
አበባ ውስጥ ከ56/ ክሊኒኮች በላይ ተጠቃሚዎችን በማስተናገድ ላይ ይገኛሉ፡፡ ስለሆነም አገልግሎቱን
ተጠቃሚዎችም አውቀውታል የሚል ግምት አለኝ፡፡››
ሲ/ር ነጻነት አባተ ከተክለሀይማኖት ጠቅላላ ሆስፒታል ያነጋገርናት አዋላጅ ነርስ ናት፡፡
‹‹ ...በሆስፒታላችን ውስጥ በወር ውስጥ ከ30-50/ የሚሆኑ ሴቶች ጽንስን የማቋረጥ አገልግሎት ሊያገኙ
ይመጣሉ፡፡ለሕክምና የሚመጡት ሴቶች አብዛኞቹ ውርጃው በተለያየ ምክንያት ጀምሮአቸው ደም እየፈሰሳቸው
የሚመጡ ሲሆን አንዳንዶች ደግሞ ተገዶ ከመደፈር ወይንም ከተለያዩ በህግ ላይ ከሰፈሩ ምክንያቶች ፣ከተፈጥሮ
ሁኔታ ጋር በተያያዘ እርግዝናው እክል ገጥሞት ጽንሱ እንዲቋረጥላቸው የሚመጡ ናቸው፡፡ ይህንን አገልግሎት
የሚፈልጉት ሴቶች በእድሜ ሲለዩ ከ19-20 አመት የሚሆኑ ወጣቶች ይበዛሉ፡፡ ይህም የሚያመለክተው ብዙዎቹ
ወጣቶች እርግዝናውን ያልፈለጉ ሲሆኑ ምክንያታቸውም መከላከያውን አለመውሰድ ወይንም ተገደው
በመደፈራቸው እና ሌሎችም ልጁን ወልደው ሊያሳድጉ የማይችሉበት ሁኔታ ላይ ያሉ ናቸው፡፡ አንዲት ሴት
ጽንስ ማቋረጥ ስለፈለገች ብቻም ጽንስ አይቋረጥም፡፡ አንዲት ሴት ጽንስ እንዲቋረጥ ጥያቄ ስታቀርብ በተደነገገው
ህግ እና በኢፊድሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስ..ር አማካኝነት ህጉን ተንተርሶ በወጣው መመሪያ መሰረት ይሆናል
የምትስተናገደው፡፡››
ቁ.3. የወንጀል ሕጉ ድንጋጌ
በአንቀጽ 551 መሰረት ‹‹ፅንስን ማቋረጥ በህግ የተፈቀደባቸው ሁኔታዎች››
2. በአንቀጽ 551 ንዑስ ቁጥር 2 ስር በፍጥነት በሚደረግ የህክምና ስራ ካልሆነ በስተቀር ሊወገድ
የማይችል ከባድና ጊዜ የማይሰጥ አደጋ ሲያጋጥም የሚፈጸም የጽንስ ማቋረጥ አያስቀጣም፡፡
በአንቀጽ 552..2.. ስር ደግሞ የሚከተለው ተደንግጎአል፡፡
..በአንቀጽ 551..1..ሀ በተገለጹት ምክንያቶች ሴትየዋ መደፈሯን ወይም ከቤተዘመድ መፀነሷን መግለጽዋ ብቻ
ፅንስ ለማቋረጥ በቂ ይሆናል..
ሕብረተሰቡ ጽንስን በማቋረጥ ሂደት ላይ ምን ተገንዝቦአል? በመንግስት የጤና ተቋማት እና በግል የህክምና
ተቋማት መካከል ያለው የሪፈራል አተገባበር ምን ይመስላል? የእናቶች መጎዳት ምን ያህል ቀንሶአል ?
ይቀጥላል

Read 13257 times