ላቭሊ የውበት ስራ ማሰልጠኛ ተቋም በተለያዩ የውበት ሥራ ሙያዎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በሚቀጥለው
ሳምንት ቅዳሜ ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ በግሎባል ሆቴል እንደሚያስመርቅ ስራ አስኪያጁ አቶ ፋሲል ሚካኤል
አስታወቁ፡፡
በእለቱ የሚመረቁት ተማሪዎች በሞዴሊንግ፣ በፀጉርና በውበት ስራ፣ በፋሽን ሾው፣ እንዲሁም በሌሎች የፈጠራ
ስራዎች የሚሰጠውን ትምህርት ተከታትለው ያጠናቀቁ ሲሆን በየዘርፉ በትምህርት ብቃታቸው ብልጫ ላሳዩ
ተማሪዎች ሽልማት እንደሚሰጥም ዋና ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
ላቭሊ የውበት ማሰልጠኛ ተቋም ላለፉት 16 ዓመታት በዘርፉ ስልጠና ሲሰጥ የቆየ ሲሆን በርካታ ዜጐችን የሙያ
ባለቤት እንዳደረገም ተገልጿል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና