Saturday, 11 October 2014 12:16

ሰንደቅ አላማውን በማያከብሩት ላይ እርምጃ ይወሰዳል ተባለ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(11 votes)

         የሰንደቅ አላማውን ክብር ለማስጠበቅ የወጣው አዋጅ ግንዛቤ ሲሰጥበት እንደቆየ የተናገሩት የሰንደቅ አላማ ቀን አከባበርና ብሄራዊ ኮሚቴ የቴክኒክ ቡድን ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ዳዊት ተፈራ፤ ህጉን ሙሉ ለሙሉ በማያከብሩት ላይ ህጋዊ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችል ገለፁ፡፡ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ቀለማት ላይ የሃይማኖትና የብሄረሰቦችን እኩልነት የሚያንፀባርቀውን ብሄራዊ አርማ በአግባቡ በማይጠቀሙ፣ በሰንደቅ አላማ አዋጅ ላይ ስለሰንደቅ አላማው ክብርና አያያዝ በዝርዝር የተመለከቱትን አንቀፆች በማያከብሩ ላይ ከዚህ በኋላ የሚመለከተው አካል ህጋዊ እርምጃ ይወስዳል ተብሎ እንደሚጠበቅ የተከበሩ አቶ ዳዊት አስታውቀዋል፡፡

ሰንደቅ አላማን በተመለከተ በተለያዩ ጊዜያት ሶስት አዋጆች ወጥተው እንደነበረ የጠቆሙት የተከበሩ አቶ ዳዊት፤ በስራ ላይ ያለው አዋጅ ቁጥር 654/2001 የአሁኑን የኢፌድሪ ሰንደቅ አላማ አለመጠቀም የህግ ጥሰት መሆኑን ይደነግጋል ብለዋል፡፡ የሰንደቅ አላማ ቀን መከበር ከጀመረ ወዲህ ህብረተሰቡ አሁን በስራ ላይ ስላለው ሰንደቅ አላማ ያለው ግንዛቤ እየዳበረ መምጣቱን የጠቀሱት የቴክኒክ ቡድኑ ሰብሳቢ፤ እንዲያም ሆኖ ህንፃዎችንና አውቶብሶችን በባንዲራ ማልበስ፣ በተገቢው ሰዓት አለመስቀልና አለማውረድ የመሳሰሉት ችግሮች እንደሚስተዋሉ ተናግረዋል፡፡

Read 4930 times