Saturday, 11 October 2014 14:11

ዋልያዎቹ የአፍሪካ ዋንጫ ህልውናቸውን ዛሬ ይወስናሉ

Written by 
Rate this item
(2 votes)
  • ውጤት ያልቀናቸው ባሬቶ፤ በሥራቸውም ውጣ ውረድ በዝቶባቸዋል፡፡
  • ምድብ 2 ለማለፍ አልጄርያ እና ማሊ የተሻለ እድል ይዘዋል፡፡
  • ዋልያዎቹና ንስሮቹ ሲነፃፀሩ፤ የኃይል ሚዛኑ ወደ ማሊ  ያጋድላል፡፡

    ዩሱፍ ሳላህ
30 ዓመቱ ነው
ትውልዱ በስዊድን ሶላና ነው፡፡
የግራ ክንፍ መስመር ላይ ይጫወታል፡
አሁን በስዊድኑ ክለብ አይኬ ሳይረስ     ይጫወታል፡፡
ከ2012 እኤአ ጀምሮ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን 9 ጨዋታዎችን አድርጎ     1 ጎል አስመዝግቧል፡፡
በዝውውር ገበያው ያለው የዋጋ ግምት 150ሺ ዩሮ ነው፡፡


አሚን አስካር
29 ዓመቱ ነው፡፡
ትውልዱ በሃረር ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፡፡
የክንፍ መስመር ላይ ይጫወታል፡፡
ከ2012 እኤአ ጀምሮ ብራነር በተባለ     የኖርዌይ ክለብ እየተጫወተ ነው፡፡
በዛሬው ጨዋታ ለኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ የሚሰለፍ ይሆናል፡፡
በዝውውር ገበያው ያለው የዋጋ ግምት 1 ሚሊዮን ዩሮ ነው፡፡

ዋሊድ አታ
28 ዓመቱ ነው፡፡
ትውልዱ በሳውዲ አረቢያ ሪያድ ነው፡፡
የመሃል ተከላካይ ሆኖ ይሰለፋል፡፡
በ2014 እኤአ ላይ ቢኬ ሃከን በተባለ     ክለብ እየተጫወተ ነው፡፡
ከ2008 እሰከ 2009 እኤአ በስዊድን ሀ21 ብሄራዊ ቡድን ሶስት ጨዋታዎች አድርጓል፡፡
በዝውውር ገበያው ያለው የዋጋ     


ለ31 ዓመታት ያለተሳትፎ የራቀበትን አህጉራዊ ውድድር ከ1 ዓመት በፊት ደቡብ አፍሪካ ባስተናገደችው 29ኛው  የአፍሪካ ንጫ በመሳተፍ ታሪኩን የቀየረው፤ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ይህን ስኬት ለመድገም አጣብቂኝ ውስጥ ነው፡፡ አንዳንድ ስፖርት ቤተሰቦች ኢትዮጵያ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ለአፍሪካ ዋንጫ ተሳትፎ የምትበቃው በውድድሩ አዘጋጅነት ብቻ መሆኑን ይገልፃሉ፡፡ በ2015 እኤአ ላይ በሞሮኮ ለሚካሄደው 31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በመላው አህጉሪቱ የሚደረገው የምድብ ማጣርያ በዚህ ሰሞን አጋማሹ ላይ ይደርሳል፡፡ ከትናንት ጀምሮ በሚካሄዱት የ3ኛው ዙር የምድብ ማጣርያ ጨዋታዎች ኢትዮጵያን ጨምሮ  10 ብሄራዊ ቡድኖች በፉክክሩ ለመቆየት ይፋለማሉ፡፡ የሰባት ግዜ ሻምፒዮኗን ግብፅን ጨምሮ ኢትዮጵያ፤ ሌሶቶ፤ቦትስዋና፤ ቶጎ፤ ሴራልዮን፤ አንጎላ  እና ሱዳን በዚህ ዙር ተጋጣሚዎቻቸውን ማሸነፍ ብቸኛ አማራጭ ይሆንባቸዋል፡፡
ማርያኖ ባሬቶና ውጣውረዳቸውፖርቱጋላዊው ማርያኖ ባሬቶ በብሄራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝነት የቆዩባቸው ያለፉት 6 ወራት ውጣውረዶች የበዙባቸው ነበሩ፡፡ ከአሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ስንብት በኋላም የዋልያዎቹ ውጤታማነት እየወረደ መጥቷል

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን በተከተለው ግልፅነት የጎደለው ቅጥራቸው በርካታ የስፖርት ቤተሰብ ደስተኛ አልነበረም፡፡ ያም ሆኖ ፌደሬሽኑ ብሄራዊ ቡድኑን ለአፍሪካ ዋንጫ የሚያሳልፉ እና በወጣቶች ላይለማከናውናቸው ስራዎች መሰረታዊ ድጋፍ በመስጠት ያግዙኛል ያላቸውን ፖርቱጋላዊ አሰልጣኝ ማርያኖ ባሬቶ በ2 ዓመት የቅጥር ኮንትራት ኃላፊነቱን ሰጥቷቸዋል፡፡ በወር 18 ሺ ዶላር የተጣራ ደሞዝ ይከፍላቸዋል፡፡ ባለፉት 6 ወራት ፌደሬሽኑ ለእኝህ አሰልጣኝ ከሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች ውጭ እስከ 109ሺ ዶላር በደሞዝ ብቻ ከፍሏል 2.16 ሚሊዮን ብር አካባቢ ማለት ነው፡፡ ይሁንና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በማርያኖ ባሬቶ ሃላፊነት ከወደቀ በኋላ ውጤት ርቆታል፡፡ እስካሁንም ነጥብ ማስመዝገብ  ልተሳካለትም፡፡ ማርያኖ ባሬቶ ከማሊ ጋር የሚገናኙበት የዛሬው ጨዋታ በአዲስ አበባ ስታድዬም ተመልካች ፊት ለሁለተኛ ጊዜ የሚያደርጉት የነጥብ ጨዋታ ነው፡፡ ብሄራዊ ቡድኑ በዚህ ወሳኝ ጨዋታ ማሸነፍ ያለው ብቸኛ አማራጭ ሲሆን ከተሸነፈ ግን የአሰልጣኙን  ቆይታ ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ይከተዋል፡፡ የ57 ዓመቱ ማርያኖ ባሬቶ በብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝነታቸው

የቆዩባቸው 190 ቀናቶች ምንም ነጥብ አለማስመዝገባቸው የሚያሳስብ ነው፡፡ ለዚህም የቀድሞው አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በሃላፊነቱ በቆዩባቸው 830 ቀናት የነበራቸው ስኬት ማስረጃ ይሆናል፡፡ በዋልያዎቹ ዋና አሰልጣኝነት 17 ጨዋታዎች ያደረጉት ሰውነት ቢሻው፣ በአንድ ጨዋታ በአማካይ 1.35 ነጥብ ይሰበስቡ ነበር፡፡ በሜዳቸው የሚያደርጓቸውን ጨዋታዎች በማሸነፍም ከሜዳ ውጭ ደግሞ ነጥብ በመጋራት እና በማሸነፍ ሰውነት ቢሻው የተሻሉ ነበሩ፡፡በእርግጥ ዋና አሰልጣኝ ማርያኖ ባሬቶ የብሄራዊ ቡድኑን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ ተሳትፎ በውጤታማ ጉዞ ለመጀመር ቢሳናቸውም በቆይታቸው አንዳንድ ምስጉን ተግባራትን አከናውነዋል፡፡ የምድብ ማጣርያውን ከመጀመራቸው በፊት ከአንጎላ ጋር የወዳጅነት ጨዋታ እንዲካሄድ ማስቻላቸው የመጀመርያው ውጤት ነው፡፡ ከዚያም ዋልያዎቹን ለ2 ሳምንት  ወደ ብራዚል በመውሰድ ልዩ አይነት ዝግጅት እንዲሰራ አድርገዋል፡፡ የብሄራዊ ቡድኑን ልምድ እና ብራንድ በማሳደግ ስኬታማ ነበር፡፡ በሌላ በኩል አንዳንድ ወጣት ተጨዋቾችን ወደ ቡድኑ በመቀላቀል ያሳዩት ቁርጠኛነት ተደንቆላቸዋል፡፡ ከላይ ከተዘረዘሩት ውጤታማ ተግባራት ዋና አሰልጣኙ በሃላፊነቱ በቆዩባቸው ባለፉት ስድስት ወራት በተለያዩ ጉዳዮች ከተጨዋቾች እና ከፌደሬሽኑ ያስቻላቸው ሁኔታዎች አሉታዊ ተፅእኖ ፈጥሮባቸዋል፡፡ ይህንኑ በተመለከተም ማርያኖ ባሬቶ በሁለቱ የምድብ ማጣርያ ጨዋታዎች ሽንፈቶች ከገጠማቸው በኋላ በተለይ ለሱፕር ስፖርት እና ለአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃናት ውጤታማ ስራ ላለማከናወን ምክንያቶች ናቸው ባሏቸው ጉዳዮች ላይ በተደጋጋሚ ቅሬታቸውን ሲገልፁ እና ሲተቹ ቆይተዋል፡፡ዋና አሰልጣኙ  በዝግጅታቸው የብሄራዊ ቡድን ተጨዋቾች የፕሮፌሽናሊዝም ደረጃ አላረካቸውም ነበር፡፡ በብዙዎቹ ተጨዋቾች የስራ ዲስፕሊን ላይ ቅሬታቸውን በተደጋጋሚ ይናገሩ ነበር፡፡ ከዚሁ ጋር አያይዘውም ብዙዎቹ የብሄራዊ ቡድን ተጨዋቾች ከስዊድን ከመጣው ዩሱፍ ሳላህ ብዙ መማር እንዳለባቸውም ሲመከሩ ሰንብተዋል፡፡ በሌላ በኩል አሰልጣኙ ከ2 ሳምንት በፊት ለሱፕር ስፖርት በሰጡት ማብራርያ ቡድናቸው በተጨዋቾች ጉዳት ክፍተት እንደበዛበት ተናግረው ነበር፡፡ በዚህም በአበበ ቢቂላ ስታድዬም በአርቴፊሻል ሳር ላይ

የተሰራው  ልምምድ ሰበብ በመሆኑ ደስተኛ አይደለሁም በማለት ወቅሰዋል፡፡  በወቅቱ በአፍሪካ ዋንጫው 3ኛ የምድብ ማጣርያ ጨዋታ ከማሊ ጋር አዲስ አበባ ላይ ከመደረጉ በፊት የወዳጅነት ጨዋታ ተገኝቶ አቋም ለመፈተሽ አለመቻሉንም ክፉኛ አማርረዋል፡፡ በተያያዘ የማሊን ቡድን ለመገምገም የሚያስችል የጨዋታ ቪድዮዎችን በፌደሬሽኑም ሆነ በግል ጥረታቸው ለማግኘት ፈልገውም ስላልሆነላቸው ቅሬታ ነበራቸው፡፡ በተጨማሪም በአንዳንድ የመጫወቻ ቦታዎች ተጨዋቾችን ማጣታቸውን ሲነቅፉም ብዙዎቹ የኢትዮጵያ ክለቦች የውጭ አገር ተጨዋቾችን በመቅጠራቸው ተተኪ ለማግኘት እንቅፋት እንደሆነባቸውም በመግለፅ ነበር፡፡ለአልጄሪያና ማሊ የተሻለ ዕድል የሚያሳዩት የምድብ 2 ሁኔታዎች
ዛሬ ከማሊ ጋር በአዲስ አበባ ስታድዬም  ለ31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ከሚደረገው የምድብ ማጣርያ 3ኛ ዙር ጨዋታ በፊት ኢትዮጵያ በምትገኝበት ምድብ ሁለት ያለምንም ነጥብ በ2 የግብ እዳ የመጨረሻ ደረጃ ላይ ናት፡፡ አልጄርያ በ6 ነጥብ እና በ2 የግብ ክፍያዎች መሪነቱን ስትይዝ፤ ማሊ በ3 ነጥብ እና በ1 የግብ ክፍያ ሁለተኛ እንዲሁም ማላዊ በ3 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃ ላይ ናቸው፡፡ በምድቡ የ3ኛ እና የ4ኛ ዙር ማጣርያ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ እና ማሊ በአዲስ አበባ እና በባማኮ፤ እንዲሁም በሌላ የምድብ 2 ጨዋታ ማላዊ እና አልጄርያ 
በብላንታየርና አልጀርስ ከተሞች የደርሶ መልስ ጨዋታዎቻቸውን ያደርጋሉ፡፡ኢትዮጵያ በምድብ ማጣርያው ሁለት ጨዋታዎች በሜዳዋ ላይ በአልጄርያ 2ለ1 ከተሸነፈች በኋላ  በሁለተኛው ዙር ጨዋታ ከሜዳዋ ውጭ በማላዊ 3ለ2 ተረታለች፡፡ የዛሬ ተጋጣሚዋ የሆነችው የምእራብ አፍሪካዋ ማሊ በአንፃሩ  በመጀመርያ ጨዋታዋ ማላዊን 2ለ0 ብትረታም በሁለተኛው ጨዋታ በአልጄርያ 1ለ0 ተሸንፋ በምድብ ሁለት ሁለተኛ ደረጃን ይዛለች፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በአልጄርያ እና በማላዊ ከደረሱበት ሽንፈቶች በኋላ ዋና አሰልጣኝ ማርያኖ ባሬቶ ከማሊ ጋር ለሚደረገው ወሳኝ የ3ኛ ዙር ማጣርያ ጨዋታቸው  23 ተጨዋቾችን በመጥራት  ከ10 ቀናት በላይ አሰርተዋል፡፡ ቡድኑ ባለፈው ማክሰኞ ብቸኛውን የአቋም መፈተሻ ግጥሚያ ያደረገው ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ነው፡፡ በዛሬው ጨዋታ ለዋልያዎቹ ከፍተኛ ክፍተት የሆነው የሳላዲን ሰኢድ አለመኖር ነው፡፡ በግብፅ ፕሪሚዬር ሊግ የመጀመርያውን የሻምፒዮናነት ክብር ለማግኘት የበቃው ሳላዲን ሰኢድ ለማሊው ጨዋታ አለመድረሱን በተመለከተ ይቅርታ ጠይቋል፡፡ አልሃሊ ከዛማሌክ ባደረጉት ጨዋታ ጉዳት የደረሰብት ሳላ እስከ ስድስት ሳምንት ከሜዳ መራቅ የብሄራዊ ቡድኑን አቅም ያዛባዋል፡፡  በውጭ አገር ክለቦች ይጫወቱ የነበሩት ያሉት ዩሱፍ ሳላህ፤ አሚን አስካር እና ዋሊድ አታ ብሄራዊ ቡድኑን በመቀላቀል ያለፉትን አምስት ቀናት ማርያም የሰሩት ይህን

ክፍተት ለመሸፈን ነው፡፡ በሳምንቱ አጋማሽ ላይ ደግሞ አራት ተጫዋቾች አሰልጣኙም መቀነሳቸው አወያይቷል
የተቀነሱት አዳነ ግርማ፣ አሉላ ግርማ፣ አንተነህ ተስፋዬ እና ግብ ጠባቂው ዮሃንስ በዛብህ ናቸው፡፡ እንደ ሱፐር ስፖርት ትንታኔ በዛሬው የኢትዮጵያና ማላዊ ጨዋታ በአማካይ መስመር ናትናኤል ዘለቀና ሽመልስ በቀለ ከጣሊያኑ የኤስ ሮማ ክለብ ተጨዋች ከሆነው ሰይዱ ኪዬቴ ጋር ይጋፈጣሉ፡፡ የዎልቨርሃምተኑ የክንፍ መስመር

ተጨዋች ባካሪ ሳኮ እና የፈርንሳዩ  ክለብ ቦርዶክስ አጥቂ የሆነው ቺዬክ ዲያቤቴ ለኢትዮጵያ ተከላካይ መስመር ፈተና እንደሚሆኑም ዘገባው አመልክቷል፡፡ ኢትዮጵያ በአጥቂ መስመር ስኬታማውን ሳላዲን ሰኢድ አለማሰለፏ እንደሚጎዳት የገለፀው ሱፕር ስፖርት፤ በግብፅ ክለብ የሚጫወተው ኡመድ ኡክሪ እና በደቡብ አፍሪካ ክለብ የሚጫወተው ጌታነህ ከበደ የማሊ ተከላካይ መስመር ለማስከፈት ከፍተኛ ፈተና ይጠብቃቸዋል ብሏል፡፡  በሌላ በኩል የበረሃዎቹ ቀበሮዎች ከማላዊ ጋር በሚያደርጓቸው የደርሶ መልስ ጨዋታዎች የምድብ 2 መሪነታቸከማሊ ጋር ያለውን ክፍተት ለማጥጭበብ በተለይ በሜዳቸው የሚደረገው ጨዋታ ወሳኝ ነው ዋልያዎቹ ከንስሮቹ ኢትዮጵያና ማሊ በታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ ዛሬ በአዲስ አበባ ስታድዬም መገናኘታቸው ውጤቱን ለመገመት
አዳጋች አድርጎታል፡፡ ጎልዶትኮም አንባቢዎቹን በማሳተፍ በሰራው ትንበያ 67 በመቶ የማሸነፍ እድል የሰጠው ለኢትዮጵያ ሲሆን ማሊ 33 በመቶ ግምት ወስዳለች፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከማሊ ጋር በሚያደርጋቸው ሁለት የደርሶ መልስ ጨዋታዎች  4 እና ከዚያም በላይ ነጥብ ካስመዘገበ በማጣርያው የሚኖረው ተስፋ

ያንሰራራል፡፡ በ3ኛው የምድብ ማጣርያ ጨዋታ በተለይ በዛሬው መሸነፍ ማለት ግን የሞሮኮን 31ኛው የአፍሪካ ዋንጫ መሳተፍ ህልም አበቃለት ማለት ነው፡፡ ኢትዮጵያና ማሊ ሁለቱን የደርሶ መልስ ጨዋታዎችን በአራት ቀናት ልዩነት ያደርጋሉ፡፡ ይህ ሁኔታ ደግሞ ልምድ በሚያነስው የኢትዮጵያ ቡድን አቋም ላይ ተፅእኖ ይፈጥራል፡፡የምድብ ማጣርያው ሲጀመር 23 ተጨዋቾችን ያሰባሰበው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በትራንስፈር ማርኬት ድረገፅ የወጣለት የተጨዋቾች ዝውውር ገበያ የዋጋ ግምቱ 725ሺ ዩሮ ነበር፡፡ ዋሊድ አታ እና አሚን አስካር ሰሞኑን ቡድኑን ከተቀላቀሉ በኋላ ግን ይህ ዋጋ ወደ 2.3 ሚሊዮን ዩሮ ከፍ ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አማካይ እድሜው 26.2 ዓመት ሲሆን በስብስቡ ያካተታቸው በውጭ አገር የሚጫወቱ ፕሮፌሽናሎች ብዛት 9 ደርሷል፡፡ ንስሮቹ በሚል ቅፅል ስም የሚጠራው የማሊ ቡድን ባለፉት ሁለት የአፍሪካ ዋንጫዎች ሶስተኛ ደረጃዎችን አከታትሎ በመውሰድ በጠንካራ ልምድ እና ተሳትፎ ላይ ይገኛል፡፡ በሄነሪ ኳስፕርዧክ

የሚሰለጥነው የማሊ ብሄራዊ ቡድንን በአማካይ መስመር የሚጫወቱት አምበሉ ሰይዱ ኪዬታ እና ሞሃመድ ሲሶኮ እንዲሁም በአጥቂ መስመር የሚሰለፈውን ሞዲቦ ማይጋ መያዙና 4­-3-3 የአሰላለፍ ታክቲክ መከተሉ ወቅታዊ አቋሙን ያከብደዋል፡፡ 27 ተጨዋቾች ያሉበት የንስሮቹ ስብስብ 23 ከአገራቸው ውጭ የሚጫወቱ ፕሮፌሽናሎችን ያካትታል፡፡ በትራንስፈር ማርኬት ድረገፅ የወጣለት የተጨዋቾች ዝውውር ገበያ የዋጋ ግምቱ  24.5 ሚሊዮን ዩሮ ሲሆን አማካይ እድሜው 25.6 አመት ነው፡፡ የማሊ ብሄራዊ ቡድን ከፍተኛ ልምድ ባለው እና የቡድኑ ዋናው አምበል በሆነው ሰይዱ ኪዬታ ብቻ ከኢትዮጵያ የላቀ ነው፡፡  በስፔኑ ክለብ ባርሴሎና ከፍተኛ ዓለም አቀፍ እውቅና የተጎናፀፈው እና በርካታ ስኬቶች ያስመዘገበው የ34 ዓመቱ ሰይዱ ኪዬታ በፈረንሳይ ሊግ 1፤ በስፔን ላሊጋ፤ በቻይና ሊግና አሁን ደግሞ በጣሊያን ሴሪኤ ላለፉት 10 የውድድር ዘመናት

በመጫወት ከፍተኛ ልምድ ያካበተ  ነው፡፡ በመሃል አማካይ መስር የሚጫወተው ኪዬታ አሁን በጣሊያኑ ክለብ ሮማ ተዛውሮ እየተጫወተ ሲሆን በሳምንት 19ሺ ፓውንድ ይከፈለዋል፡፡ ነው፡፡ በትራንስፈር ማርኬት ድረገፅ በተገኘ መረጃ መሰረት ኪዬታ ከ5 አመት በፊት በዝውውር ገበያው የዋጋ ተመኑ 16 ሚሊዮን ዩሮ ነበረ፡፡ አሁን ግን ግምቱ ወደ 1 ሚሊዮን ዩሮ ወርዷል፡፡ ከ2000 እኤአ ጀምሮ በማላዊ ብሄራዊ ቡድን ሲጫወት 90

ጨዋታዎች አድርጎ 23 ጎሎች በስሙ አስመዝግቧል፡፡ በባርሴሎና ስኬታማ ቆይታ የነበረው ኪዬታ ሁለት

የሻምፒዮንስ ሊግ፤ እና የላሊጋ ዋንጫዎችን ጀምሮ 14 ዋንጫዎችን በመሰብሰብ ታሪክ የሰራ ነው፡፡

Read 4775 times