በዘራፍ ፊልም ፕሮዳክሽን የተዘጋጀው “ቀዮ” የፍቅር ኮሜዲ ፊልም ዛሬ በአዲስ አበባ እና በሌሎች ከተሞች ይመረቃል፡፡ ዋነኛ የምርቃት ሥነ ሥርአቱን በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ትያትርና ባህል አዳራሽ ያደረገውን “ቀዮ”ን የፃፈው ኤልያስ ሙላለም ሲሆን አዘጋጁ ቢኒያም ዮሐንስ ነው፡፡ የ100 ደቂቃ ፊልሙን ለማዘጋጀት አምስት ወር የፈጀ ሲሆን ሜላት ነቢዩ፣ ኤቪያን አማኑዔል፣ ዘነቡ ገሠሠ፣ ቅድስት አስመላሽና ሌሎች ተውነውበታል፡፡ በሌላም በኩል “በዋን ፕላኔት” ፊልም ፕሮዳክሽን የተዘጋጀው “ሳመኝ” ልብ አንጠልጣይ ፊልም በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ነገ የሚመረቅ ሲሆን ጥር 7/2004 ዓ.ም ደግሞ በልዩ ፕሮግራም በብሔራዊ ትያትር እንደሚመረቅ ታውቋል፡፡ የፊልም ስክሪፕቱን ኪሩቤል ሳሙኤል የፃፈው ሲሆን ዮሐንስ ዳምጤ አዘጋጅቶታል፡፡ የ105 ደቂቃ ፊልሙ በዘጠኝ ወራት የተሰራ ሲሆን የሺ ደምበላሽ፣ አለባቸው መኮንን፣ ሰገን ይፍጠር እና ሌሎች ተውነውበታል፡፡