በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ ለአድማጭ ጆሮ የደረሱት የድምፃዊ ደምስ ዴሲሳ “ከሚሴ አሪመሩ”፣ “ጅማአሻ” እና “አንሲመሌ” የተሰኙ ሶስት ነጠላ ዜማዎች ተወዳጅነትን እንዳተረፉለት ድምፃዊው ተናገረ፡፡
“ከሚሴ አሪመሩ” የተባለው በወሎ ከሚሴ ስልት የተሰራው የፍቅር ዘፈን ይበልጥ እንደተወደደለት የገለጸው ድምፃዊው፤ የነጠላ ዜማዎቹ ተቀባይነት ሙሉ አልበሙን ለመስራት እንዳበረታታው ገልጿል፡፡
ዜማና ግጥማቸው በታዋቂው የባህል ድምፃዊ ሰማኸኝ በለውና ሙሉጌታ ዜና የተሰሩት ነጠላ ዜማዎቹ በሙሉጌታ ዜና ተቀናብረው በዮናስ መሃሪ መዋሃዳቸው ታውቋል፡፡ ድምፃዊ ደምስ ዴሲሳ ከዚህ ቀደም የመጀመርያ ሙሉ አልበሙን ለአድማጭ ማድረሱ ይታወቃል፡፡
Monday, 20 October 2014 08:30
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና