Print this page
Monday, 03 November 2014 09:04

የፈነዳችው የናሳ ሮኬት ስብርባሪዎች የጤና ጉዳት ያደርሳሉ ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ባለፈው ማክሰኞ በምስራቃዊ ቨርጂኒያ ውስጥ ከሚገኝ ማዕከል ተነስታ ወደ ህዋ ጉዞ በጀመረች በሰከንዶች ጊዜ ውስጥ የፍንዳታ አደጋ የደረሰባት ሰው አልባ ሮኬት ስብርባሪዎች በሰዎች ላይ የጤና ጉዳት ስለሚያደርሱ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ባለሙያዎች አስጠነቀቁ፡፡
የጠፈር ምርምር ቁሳቁሶችን ወደ አለማቀፉ የጠፈር ጣቢያ ለማጓጓዝ አወዛጋቢ በሆነ ሁኔታ ከናሳ ጋር ስምምነት ላይ የደረሰው “ኦርቢታል ሳይንስስ” የተባለው ተቋም ምክትል ፕሬዚዳንት ፍራንክ ከልቤርስቶን፤ በድንገተኛ ፍንዳታ በእሳት የጋየችውን ሮኬት ስብርባሪ መንካት፣ ሮኬቷ ጭናቸው በነበሩ አደገኛ ቁሳቁሶች ምክንያት ለጤና እክል የሚያጋልጡ ስለሆኑ አስፈላጊው ጥንቃቄ እንዲደረግ መምከራቸውን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
“አደጋው በተከሰተበት አካባቢ ለሚንቀሳቀሱ ሁሉ የማስጠንቀቂያ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ፡፡ አደጋ የደረሰባት ሮኬት በርካታ አደገኛ ቁሳቁስ ጭና ነበር፡፡ ስብርባሪዎችን ፍለጋ ወደ ስፍራው መንቀሳቀስ አደጋ አለው፡፡” ብለዋል ከልቤርስቶን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፡፡
ማንም ሰው በአካባቢው ወድቆ ያገኘውን ማንኛውንም አይነት ቁስ ከመንካት እንዲቆጠብና ሌሎችም ከአካባቢው እንዲርቁ በማድረግ፣ ለሚመለከታቸው የስራ ሃላፊዎች ጥቆማ እንዲሰጥም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
2ሺ 200 ኪሎ ግራም የሚመዝን ጭነት የያዘ መንኮራኩር ይዛ ጉዞ የጀመረችውን ሮኬት ለአደጋ ያጋለጣት ምክንያት እስካሁን አልታወቀም፡፡ ሮኬቷና መንኮራኩሩ 123 ሚሊዮን ፓውንድ እንደሚያወጡ ዘገባው ገልጿል፡፡

Read 2095 times
Administrator

Latest from Administrator