Saturday, 08 November 2014 10:47

የቴሌኮሙኒኬሽን መሳሪያዎችን በህገወጥ መንገድ ያስገቡ ከ70 በላይ ተጠርጣሪዎች ተያዙ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

        ለተለያዩ የቴሌኮሙኒኬሽን ሥራዎች የሚያገለግሉ መሣሪያዎችን በህገወጥ መንገድ ወደ አገር ውስጥ ሲያስገቡ ተገኝተዋል የተባሉ 3 የውጭ አገር ዜጐችና አራት የኢትዮ ቴሌኮም ሰራተኞችን ጨምሮ 70 የሚደርሱ ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡ አገሪቱን በሚሊዮን የሚገመት ገቢ አሣጥተዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች፤ በህገወጥ መንገድ ወደ አገር ውስጥ የገቡ የተለያዩ ለቴሌኮሙኒኬሽን ሥራ የሚያገለግሉ መሣሪያዎችን በአዲስ አበባ፣ አዋሣ ጭሮ፣ ድሬዳዋ፣ ሐረርና ጅግጅጋ ከተሞች ጥቅም ላይ አውለዋል ተብሏል፡፡ ፖሊስ፤ ተጠርጣሪዎቹ ህገወጥ ድርጊታቸውን በውጭና በሀገር ውስጥ በተደራጀ ሁኔታ ሲያከናውኑ እንደቆዩ ደርሼበታለሁ ብሏል፡፡
ህብረተሰቡ በሚኖርበት አካባቢ ለየት ያሉ እንደ ትናንሽ የሳተላይት መቀበያ ያሉ የቴክኖሎጂ መጠቀሚያና መሰል መሣሪያዎች ተተክለው ሲያይ በየአካባቢያቸው ለሚገኝ የፖሊስ አካል ወይም ለኢትዮ ቴሌኮም ነጻ የጥሪ ማዕከል 994 በመጠቀም ጥቆማ ማቅረብ ይችላል ተብሏል፡፡

Read 2586 times