Saturday, 15 November 2014 11:00

ኢቦላ - የዛሬ 38 ዓመት

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ቤልጂየማዊው ፒተር ፒዮ የኢቦላ ቫይረስን ለመጀመሪያ ጊዜ ከመረመሩና ለቫይረሱም ስያሜ ከሰጡ ሳይንቲስቶች አንዱ ነው፡፡ በቅርቡ  ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ የሰጠውን ቃለመጠይቅ ለጋዜጣው በሚመች መልኩ አቅርበነዋል መልካም ንባብ፡፡
“እሼ እዛው ነዋሪ ገበሬ ነው፡፡ ሞቅ ይለዋል! አንዱ ገንዘብ ሰጥቶ ምግብ በሳህን አርጎ ሂድ ወደሚስትህ ይለዋል፡፡
ይሄዳል፡፡ ግን በጨለማ በቀጭኑ ድንጋያማ የዘሙቴ መንገድ ሲሄድ ገንዘቡ ይጠፋዋል፡፡ ሳህኑን መሬት አስቀምጦ ገንዘብ
ፍለጋ ይመለሳል፡፡ ገንዘቡ የለም፡፡


ያኔ የኢቦላ ቫይረስ እንዴት እንደታወቀ ንገረኝ?
እ.ኤ.አ በ1976 በመስከረም ወር በአንዱ ቀን የሳቤና አየር መንገድ አውሮፕላን አብራሪ የነበረ ሰው በወቅቱ ዛየር በሚባለው በአሁኑ አጠራር ኮንጐ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ከሚገኝ አንድ ሃኪም በጥንቃቄ የተላከ የደም ናሙና ወደ ቤልጂየም ይዞልን መጣ፡፡ የደም ናሙናው በዛየር ያምቡኩ በተባለ ቦታ በበጎ አድራጎት ስራ ላይ ከነበሩ የቤልጂየም መነኮሳት የኣንዷ ነበር፡፡ መነኩሲቷ በማይታወቅ ህመም እየተሰቃየች የነበረ ሲሆን የደም ናሙናው ሲላክልንም ቢጫ ወባ ሊሆን ይችላል በሚል ግምት ነበር፡፡
በአሁኑ ወቅት የኢቦላ ቫይረስ ምርመራ የሚካሄደው እጅግ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ነው፡፡ ያኔ እንዴት ነበር?
ቫይረሱ ምን ያህል አደገኛ እንደነበር አናውቅም ነበር፡፡ በከፍተኛ ጥንቃቄ የሚሰራበት ላቦራቶሪም ቤልጂየም ውስጥ አልነበረም፡፡ የምንሰራው የተለመደውን ነጭ ጋውንና ጓንት አድርገን ነበር፡፡
የመነኩሲቷ የደም ናሙና ከቢጫ ወባ ጋር ግንኙነት ነበረው?
አልነበረውም፡፡ ህመሟ ከቢጫ ወባና ከታይፎይድ ጋር ግንኙነት ከሌለው ምን ሊሆን ይችላል በሚል ጥረታችንን ቀጠልን፡፡ ከተላከው ናሙና ላይ ቫይረሱን ለመለየት አይጦችንና ሌሎች የላብራቶሪ እንስሳቶችን ወጋናቸው፡፡ ለብዙ ቀናት በእንስሳቶቹ ላይ ምንም አይነት ለውጥ ስላላየን ምናልባት ናሙናው ሲመጣ በቅዝቃዜ እጦት ተጎድቶ ሊሆን ይችላል ብለን አስበን ነበር፡፡ በኋላ ግን እንስሳቱ ተራ በተራ መሞት ሲጀምሩ ናሙናው ገዳይ ነገር እንዳለው አረጋገጥን፡፡
ከዚያስ ምን አደረጋችሁ?
በትንሽ ጊዜ ውስጥ ሌላ የመነኩሲቷን ደም የያዘ ናሙና መጥቶልን በኤሌክትሮን ማይክሮስኮፕ ለመመርመር ስንዘጋጅ፣ የአለም የጤና ጥበቃ ድርጅት ናሙናውን ከፍተኛ ጥንቃቄ ወዳለበት እንግሊዝ ወደሚገኝ ላቦራቶሪ እንድንልከው መመሪያ ሰጠን፡፡ ነገር ግን አለቃዬ የፈለገው ነገር ቢሆን ስራችንን ማጠቃለል አለብን ብሎ ስላመነ ናሙናውን አልላክነውም፡፡ በወቅቱ አለቃዬ ናሙናውን ለመመርመር ሲቀበል እጁ በጣም ይንቀጠቀጥ ስለነበር፣ ከናሙናው ወደ መሬትና ወደ አንዱ ባልደረባችን እግር ላይ  ፈስሶ ነበር፡፡ ሆኖም ጓደኛችን ጠንካራ ቆዳ ጫማ አድርጎ ስለነበር ምንም አልተፈጠረም፡፡
በመጨረሻ የቫይረሱን ምንነት አወቃችሁ?
አዎ፡፡ ለመመርመር ብዙ ጊዜ የፈጀበን ቫይረስ ትልቅና ረዘም ያለ መስሎን ነበር፡፡ ቫይረሱ ከቢጫ ወባ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የለውም፡፡ ይልቁንም በ1960ዎቹ  ጀርመን ማርበርግ ውስጥ ብዙ የላቦራቶሪ ባለሙያዎችን ህይወት ከቀጠፈው ማርበርግ ቫይረስ ጋር የሚመሳሰል ነበር፡፡
ስጋት አልፈጠረባችሁም ነበር?
ስለ ማርበርግ ቫይረስ ምንም አላውቅም ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ተማሪዎቼን ስለዚያ ወቅት ስነግራቸው ስለ ድንጋይ ዘመን የማወራላቸው ይመስላቸዋል፡፡ ላይብረሪ ሄጄ የቫይሮሎጂ አትላስ ላይ ማየት ነበረብኝ፡፡
የእኛ ውጤት በታወቀ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሲዲሲ ባወጣው መረጃ ማርበርግ እንዳልሆነ ነገር ግን ተመሳሳይነት ያለው ቫይረስ እንደሆነ ገለፀ፡፡ በወቅቱ ያምቡኩና በአቅራቢያ ባሉ ቦታዎች ብዙ ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተው ነበር፡፡
ወደ ዛየር ከሄዱት ሳይንቲስቶችም አንዱ ነበርክ አይደል?
አዎ፡፡ የሞተችውን መነኩሲት ጨምሮ ትንሽ ሆስፒታል ከፍተው ይሰሩ የነበሩት ቤልጂየሞች ስለነበሩ የቤልጂየም መንግስት ባለሙያ ለመላክ ሲወስን ወዲያው ፈቃደኝነቴን ገለፅኩ፡፡ ያኔ 27 አመቴ ነው፡፡ የወጣትነት ዘመን ጀብድ በለው፡፡
እንዴት ደፈርክ?
ከዚህ በፊት በአለም ያልታየ ገዳይ በሽታ የምናክም ቢሆንም ቫይረሱ ከሰውነት በሚወጡ ፈሳሾች እንደሚተላለፍ አናውቅም ነበር፡፡ ጋውንና ጓንት እንዲሁም ሞተርሳይክል አሽከርካሪዎች የሚያደርጉትን መነፅር ብቻ ነበር የምንጠቀመው፡፡ ኪንሻሳ የገዛሁትን የጋዝ ማስክ ደግሞ በሙቀቱ ምክንያት ማድረግ አልችልም ነበር፡፡ ያስፈራኝ የነበረው ነገር የደም ናሙና ስወስድ የደም ንክኪ ተፈጥሮ በበሽታው እንዳልያዝ ነበር፡፡
ግን በበሽታው ከመያዝ  አመለጥክ?
አዎ፡፡ በእርግጥ በአንድ አጋጣሚ ከፍተኛ ትኩሳት ፣ የራስ ምታትና ተቅማጥ ይዞኝ በቃ ተያዝኩ ብዬ ከክፍሌ ሳልወጣ፣ ለቀናት እንቅልፍ በአይኔ ሳይዞር አሳልፌያለሁ፡፡ በኋላ ግን እየተሻለኝ መጣ፣ የታመምኩት በጨጓራ ኢንፌክሽን ነበር፡፡ በህይወት ከሚያጋጥሙ ፈተናዎች የተሻለው ነው፡፡ ሞት ሲመጣ በአይንህ ታየዋለህ፤ ነገር ግን ለመዳን እድል አለ፡፡
ለቫይረሱ ስያሜ ከሰጡት ተመራማሪዎች አንዱ አንተ ነህ፡፡ ለምን ኢቦላ ተባለ?
ስያሜው በተሰጠበት ምሽት የተመራማሪ ቡድኑ አንድ ላይ እየተወያየ ነበር፡፡ ቫይረሱ በተከሰተበት በያምቡኩ መሰየሙ ቦታውን እስከ ወዲያኛው ያገለዋል ብለን አመንን፡፡ እናም አሜሪካዊው የቡድኑ መሪ  በአቅራቢያችን በሚገኘው ወንዝ ይሰየም አለ - ፊትለታችን ከተንጠለጠለው ካርታ ላይ የኢቦላን ወንዝ ተመልክቶ፡፡ ነገር ግን የተሰቀለው ካርታ ትንሽና የተዛቡ ነገሮች ነበሩበት፡፡ ኢቦላም በአቅራቢያ የሚገኝ ወንዝ እንዳልሆነ ብናረጋግጥም ስያሜው ግን ኢቦላ እንደሆነ ቀረ፡፡
ለቫይረሱ መዛመት የቤልጂየም መነኩሲቶች ድርሻ አለበት ይባላል...
በወቅቱ መነኩሲቶቹ በሚሰሩበት ሆስፒታል ለነፍሰጡር ሴቶች የቫይታሚን ክትባት ይሰጡ ነበር፤ ነገር ግን የመርፌው ንፅህና የተጠበቀ አልነበረም፡፡ በዚህም ምክንያት ብዙ ነፍሰጡሮች በቫይረሱ እንዲያዙ አድርገዋል፡፡ በቅርቡ በምእራብ አፍሪካ ለተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ሆስፒታሎች የመጀመሪያውን ድርሻ ይወስዳሉ፡፡
ከያምቡኩ በኋላ ላለፉት ሰላሳ አመታት ኤድስ ላይ አተኩረህ ሰርተሃል፡፡ ኢቦላ አሁን አዲስ ስጋት ሆኗል፡፡ የአሜሪካን ሳይንቲስቶች በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በበሽታው ሊጠቁ እንደሚችሉ ገልፀዋል፡፡ ወረርሽኙ በዚህ ደረጃ ትጠብቀው ነበር?
በፍፁም አልነበረም፡፡ እንዲያውም ተቃራኒ ነበር፡፡
ኢቦላ እንደ ወባና ኤድስ ችግር ፈጣሪ አልነበረም፤ ምክንያቱም ሲከሰት የነበረው በጣም በተወሰኑ ገጠራማ አካባቢዎች ነው፡፡ ባለፈው ሰኔ ወደ ትላልቅ ከተሞች መግባቱን ስሰማ ከወትሮው የተለየ ነገር እንደተፈጠረ ገባኝ፡፡ በተመሳሳይ ወር የድንበር የለሹ የሀኪሞች ቡድን ስጋቱን ከገለፀ በኋላ እጅግ አሳሰበኝ፡፡
የአለም የጤና ድርጅት ምላሹን የሰጠው ዘግይቶ ነው፡፡ ለምንድን ነው?
በአንድ በኩል የድርጅቱ የአፍሪካ ቢሮ ብቃት ባላቸው ሳይሆን በፖለቲካ ሹመኞች የተሞላ ነው፡፡
በሌላ በኩል ጄኔቫ ያለው የድርጅቱ ዋና ቢሮ በበጀት ቅነሳ ምክንያት ችግር ያለበት ሲሆን በተለይ ደግሞ የድንገተኛ ወረርሽኞች ዲፓርትመንቱ በጣም የተዳከመ ነው የተዳከመ ነው የተጎዳ ነው፡፡ ከነሐሴ ወር በኋላ ግን ድርጅቱ የመሪነት ሚናውን መጫወት ጀምሯል፡፡
በዛየር የመጀመሪያው ወረርሽኝ ሲከሰት የሆስፒታሎች የንፅህና መጓደል አስተዋፅኦ አድርጎ ነበር፡፡ አሁንም ተመሳሳይ ነገር ነው ያለው፡፡ ሉዊ ፓስተር “ሁሉም ነገር ያለው ባክቴሪያና ቫይረስ ላይ ነው” ብሎ ነበር፡፡ በዚህ ትስማማለህ?  
በጣም እስማማለሁ! ኤችአይቪ አሁንም አለ፡፡ ለንደን ውስጥ ብቻ በቀን አምስት ግብረሰዶማውያን በቫይረሱ ይያዛሉ፡፡ ቁጥራቸው በዛ ያሉ ባክቴሪያዎች መድሀኒት የመቋቋም አቅማቸው እየጨመረ ነው፡፡ በባክቴሪያና በቫይረስ ላይ አሸናፊነትን ለመቀዳጀት ገና ብዙ ይቀረናል፡፡
 በሌላ በኩል ደግሞ ይህ እውነት ብዙ እንድሰራ ያበረታታኛል፡፡ ለዚህም ነው በአለም ላይ ያሉ ሀያላን ለምእራብ አፍሪካ አገራት በቂ እርዳታ እንዲያደርጉ የተቻለኝን እያደረግሁ ያለሁት፡፡

Read 3320 times