Saturday, 22 November 2014 12:15

በኤችአይቪ ምርመራ ጊነስ ቡክ ላይ ለመመዝገብ ጥረት ተጀመረ

Written by  መታሰቢያ ካሳዬ
Rate this item
(3 votes)

ኢትዮጵያን በኤችአይቪ ምርመራና የምክር አገልግሎት ጊነስ ቡክ ኦፍ ሪከርድ ላይ ለማስመዝገብ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ዩኤንኤድስ የተባለ ድርጅት አስታወቀ፡፡
በስምንት ሰዓት ጊዜ ውስጥ ለሁለት ሺህ ሰዎች ነፃ የኤችአይቪ ምርመራና ምክር አገልግሎት በመስጠት፣ አገሪቱን በጊነስ መዝገብ ላይ ለማስመዝገብ የሚደረገው ጥረት፣ በጋምቤላ ክልል ህዳር 21 ቀን 2007 ዓ.ም እንደሚከናወን አዘጋጆቹ ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡
ከሁለት ዓመት በፊት በተመሳሳይ ሁኔታ የአለም ክብረወሰን ሆኖ በጊነስ መዝገብ ላይ የሰፈረው በአሜሪካና በአርጀንቲና ለ1380 ሰዎች የተሰጠው ነፃ የምርመራና የምክር አገልግሎት እንደሆነ ታውቋል፡፡ ጥረቱ ለአገሪቱ በጐ ገፅታ ከማላበስ ባሻገር በክልሉ በኤችአይቪ ዙሪያ ያለውን ግንዛቤ ለማሳደግ ያግዛል ተብሏል፡፡

Read 2274 times