Saturday, 22 November 2014 12:23

አዋሽ ኢንሹራንስ አዲስ ሶፍትዌር መጠቀም ጀመረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

አዋሽ ኢንሹራንስ ኩባንያ በአገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው አዲስ የኢንሹራንስ ሶፍትዌር አሰርቶ ስራ ላይ ማዋሉን አስታወቀ፡፡ ኩባንያው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ ውጤማታና ቀልጣፋ አገልግሎት ለደንበኞቹ ለመስጠት፣ የተቀናጀ የጠቅላላ መድን የመረጃ ሥርዓት (General Insurance Information System - Glls) ሶፍትዌር ማሰራቱን የጠቀሱት የኩባንያው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ፀጋዬ ከሚሴ፤ ሶፍትዌሩን የሰራው የህንዱ ኩባንያ ኢንፎዥን፣ አማካሪው ደግሞ አገር በቀሉ ናሽናል ኮንሰልቲንግ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ዛሬ የደረስንበት ስኬት በሀገሪቷ የኢንሹራንስ ኢንዱስትሪ ውስጥ የተሟላ የቴክኖሎጂ መፍትሄ በመፍጠር ረገድ እንደ መልካም መነሻ ይታያል ያሉት ሥራ አስኪያጁ፤ በየክልሉ ያሉት ቅርንጫፎቻችን በሙሉ ይህንን አዲስ ሶፍትዌር ስለሚጠቀሙና የመረጃ ሥርዓቱ በኔትዎርክ የታገዘ በመሆኑ፣ የኩባንያው የሥራ አመራሮች የእያንዳንዱን ቅርንጫፍ ዝርዝር ሥራ በመከታተል ተገቢውን ድጋፍ በፍጥነት ይሰጣሉ ብለዋል፡፡ በመረጃ ሥርዓቱ አማካይነት ሪፖርቶችን በአጭር ጊዜ ውስጥ በማግኘት መረጃና ዕውቀት ላይ የተመሰረተ የማኔጅመንት ውሳኔ መስጠት እንደሚቻል ገልጸው፤ በውል ሰነዶች ውስጥ ያሉ መረጃዎች ሁሉ በሲስተሙ ውስጥ ስለተጠቃለሉ የሁሉም  ደንበኞች የውል፣ የካሣ፣ የጠለፋ ዋስትና፣ የገበያ ልማትና የፋይናንስ መረጃዎች በቀላሉ የሚናበቡ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
በውላቸው መሰረት ሶፍትዌሩን የሰራውና አማካሪው በየጊዜው ማሻሻያ እንደሚያደርጉና ይሄም ለኩባንያው ራዕይ መሳካት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት የገለፁት ሥራ አስኪያጁ፤ በዚህም “ግንባር ቀደምና ተመራጭ መድን ሰጪ መሆን” የሚለውን የኩባንያችንን ራዕይ እናሳካለን ብለዋል፡፡ ለሶፍትዌሩ 2.5 ሚሊዮን፣ ለሃርድዌሩ ደግሞ 3 ሚሊዮን ብር ወጪ መደረጉንም ገልጸዋል፡፡  

Read 1600 times