Saturday, 13 December 2014 10:20

ኢዴፓ ነገ በመቀሌ ህዝባዊ ስብሰባ ያደርጋል

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(10 votes)

የኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) በነገው እለት በመቀሌ ከተማ ህዝባዊ ስብሰባ እንደሚያደርግ አስታወቀ፡፡
በመቀሌ በሚካሄደው ስብሰባ ላይ በግንቦቱ ምርጫ በኑሮ ውድነት፣ በሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ጥሰት ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግ የጠቆመው ፓርቲው፤ በስብሰባው ላይ የፓርቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጫኔ ከበደን ጨምሮ በርካታ አመራሮች እንደሚገኙ አስታውቋል፡፡ ፓርቲው በአዲስ አበባና በባህር ዳር በተከታታይ ሊያካሂዳቸው የነበሩ ህዝባዊ ስብሰባዎች እንደተሠናከሉበት ጠቁሞ ባለፈው ሳምንት በባህር ዳር ከተማ ካቀደቸው ስብሰባዎች አንደኛው ተሣክቶለት ህዳር 27 በሙሉአለም የባህል ማዕከል በአጥጋቢ ሁኔታ ማከናወኑን አስታውቋል፡፡
በስብሰባው ላይ 1500 የሚደርሱ አባላትና ደጋፊዎች የተሳተፉ ሲሆን በምርጫ፣ በሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች እና በኑሮ ውድነት ዙሪያ ውይይት መካሄዱን ፓርቲው ጠቁሟል፡፡
ከዲሞክራሲያዊ መብቶች ዋነኛው የመሰብሰብ መብት ነው ያለው ፓርቲው፤ በቀጣይ በአዲስ አበባም ሆነ በተቀሩት የሃገሪቱ ክልል ከተሞች ተከታታይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን እንደሚያዘጋጅ አስታውቋል፡፡

Read 2058 times