Saturday, 13 December 2014 11:20

“ውቤ ከረሜላ” ልብወለድ መፅሀፍ ለንባብ በቃ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(24 votes)

በሁለት ትውልዶች የፍቅር፣ የባህልና የወግ ሁኔታ ላይ የሚያጠነጥነው “ውቤ ከረሜላ” ልብወለድ መፅሃፍ (ቁጥር አንድ) ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡ በደራሲ ኤልያስ ማሞ የተፃፈው ልቦለድ፤ በዋናነት በኃይለ ሥላሴና በደርግ ዘመን የነበሩ የፍቅር፣ የጋብቻ፣ የወግና የባህል ሁነቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን በልማት ምክንያት እየተቀየሩና እየጠፉ ስላሉ እንደነ ውቤ በረሃ ያሉ አካባቢዎችንም ይዳስሳል ተብሏል፡፡ ልብወለዱ ለደራሲው ሁለተኛው ስራው ሲሆን ከዚህ ቀደም “እንጦሽ” በተሰኘ የአጫጭር ልብወለዶች ስብስብ ውስጥ ሥራው ተካትቶለታል፡፡ “ውቤ ከረሜላ ቁጥር 2” በመጪው ሰኔ፣ ቁጥር 3 ደግሞ የዛሬ ዓመት ገደማ ለአንባቢ እንደሚደርስም ደራሲው ገልጿል፡፡ የአሁኑ ልብወለድ በ244 ገፆች የተቀነበበ ሲሆን ለአገር ውስጥ በ50 ብርና ለውጭ አገር በ19 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 8619 times