Saturday, 10 January 2015 09:44

ኢትዮጵያዊቷ በሳዑዲ የሞት ቅጣት ተፈረደባት

Written by 
Rate this item
(7 votes)

ፍርዱ በአፋጣኝ ተግባራዊ እንዲደረግ ተጠይቋል
በሳዑዲ አረቢያ ከሁለት አመታት በፊት አሰሪዋን በመጥረቢያ ደብድባ ገድላለች በሚል ክስ የተመሰረተባት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ፤ በጣይፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የሞት ፍርድ እንደተፈረደባት አረብ ኒውስ ከትናንት በስቲያ ዘገበ፡፡
በደቡባዊ ጣይፍ ግዛት በምትገኘው ሙሳይላት የተባለች መንደር በቤት ሰራተኛነት ስታገለግል የነበረችውና ስሟ ያልተገለጸው ኢትዮጵያዊቷ፣ ፍርዱን በመቃወም ይግባኝ መጠየቋን የጠቆመው ዘገባው፣ የመካ ፖሊስ ቃል አቀባይ በበኩላቸው፤ ግለሰቧ ዝርፊያ ለመፈጸም በማሰብ ወንጀሉን እንደፈጸመች ተናግረዋል፡፡
በ30ዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ እንደምትገኝ የተነገረላት ኢትዮጵያዊቷ፤ በስግደት ላይ በነበረችዋ አሰሪዋ ላይ ወንጀሉን ከፈጸመች በኋላ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሏንና በወቅቱም በእጇ ላይ 7 ሺህ የሳዑዲ ሪያል (ገንዘብ) መገኘቱን ዘገባው ያስረዳል፡፡
የሟቿ ባለቤት በበኩሉ፤ በፍርድ ቤቱ ውሳኔ እንደተደሰተ ገልጾ፣ የሞት ፍርዱ በአፋጣኝ ተግባራዊ እንዲደረግ መጠየቁምን አረብ ኒውስ አክሎ ገልጿል፡

Read 2490 times