Saturday, 24 January 2015 11:51

የደ/አፍሪካው ስታንዳርድ ባንክ በኢትዮጵያ ቢሮ ሊከፍት ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የደቡብ አፍሪካው ስታንዳርድ ባንክ በመጪው መጋቢት ወር መጨረሻ በኢትዮጵያ ተወካይ ቢሮ
ሊከፍት መሆኑን ቬንቸርስ አፍሪካ ድረገጽ ዘገበ፡፡የአገሪቱ የፋይናንስ ህግ የውጭ አገራት ባንኮች በመስኩ እንዳይሰሩ የሚከለክል እንደመሆኑ፣ ባንኩ ኢትዮጵያ የሚከፍተው ተወካይ መስሪያ ቤት የገንዘብ ብድርና ቁጠባን የመሳሰሉ ስራዎችን እንደማያከናውን የስታንዳርድ ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት ጣይቱ ወንድወሰንን ጠቅሶ ዘገባው ገልጿል፡፡በአዲስ አበባ የሚከፈተው ቢሮ ስታንዳርድ ባንክ በአገሪቱ ከሚገኙ ኩባንያዎች ጋር መልካም የስራ ግንኙነት ለመፍጠር የሚያስችሉ ስራዎችና የገበያ ጥናቶች የሚከናወንበት እንደሚሆን የገለጸው ዘገባው፤ የቢሮው መከፈት ባንኩ በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት ስራዎችን ለማከናወን ፍላጎት ላላቸው ደንበኞቹ የማማከር አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዘውም አስረድቷል፡፡

Read 1312 times