Print this page
Saturday, 24 January 2015 11:54

የኤርትራ ካቶሊክ ቤ/ክርስትያን የራሷ ሊቀጳጳስ ተሾመላት

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

•    በኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ስትተዳደር ቆይታለች
ከሀያኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ አንስቶ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አካል የነበረችው የኤርትራ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሰሞኑን  በራሷ እንድትተዳደር የተወሰነ ሲሆን  አባ መንግስተአብ ተስፋማሪያም የመጀመሪያው የኤርትራ ሊቀጳጳስ ሆነው ተሾሙ፡፡ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ከተነጠለች በኋላም የኤርትራ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን  በአዲስ አበባ ቅርንጫፍና በአንድ የጳጳስ ጉባኤ ስር ስትተዳደር የቆየች ቢሆንም ሰሞኑን ከቫቲካን የወጣ መረጃ፤ የሮማ ካቶሊካዊት ቤ/ክርስትያን አቡን ጳጳስ ፍራንሲስ የኤርትራ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በአስመራ ቅርንጫፍ ራሷን ችላ እንድትተዳደር መወሰናቸውንና አባ መንግስተአብ ተስፋማሪያምን ሊቀጳጳስ አድርገው መሾማቸውን ጠቁሟል፡፡
የኤርትራ የመጀመሪያው የካቶሊክ ሊቀጳጳስ ሆነው የተሾሙት የአስመራ  ሀገረስብከት ጳጳስ  የነበሩት አባ መንግስተአብ ተስፋማርያም፤ ኤርትራ የ23ኛ አመት የነፃነት በአሏን ስታከብር “ወንድምህ የት ነው” በሚል ርዕስ በወቅታዊ የኤርትራ ሁኔታ ላይ በተለይ የወጣቶችን ስደት የተመለከተ  ሀተታና ጥያቄዎችን የያዘ ሰነድ ለፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ካስረከቡ አራት ጳጳሳት  አንዱ ነበሩ፡፡የጳጳሱን መሾም ተከትሎም የኤርትራ መንግስት ደጋፊ በሆኑ ድረገፆች አቡነ መንግስተአብ ተስፋማርያምን የሚያጥላሉ አስተያየቶች እየተሰነዘሩ ይገኛሉ፡፡ ኢትዮጵያና በኤርትራ የተደረገውን ጦርነት ተከትሎ  የሁለቱ አገራት ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያናት ስብሰባዎቻቸውን በኢትዮጵያም ሆነ በኤርትራ ሊያደርጉ ባለመቻላቸው በሮም ሲያካሂዱ መቆየታቸው ታውቋል፡፡

Read 2114 times
Administrator

Latest from Administrator