ላለፉት ሃምሳ አመታት ተስለው የተጠራቀሙ የሰዓሊ ወርቁ ጐሹ የስዕል ስራዎች ለዕይታየ ማቀርቡበት “ላይት” የተሰኘ የስዕል አውደ ርዕይ የፊታችን አርብ ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ በብሔራዊ ሙዚየም አርት ጋለሪ ይከፈታል፡፡
በዚህ አውደ ርዕይ እጅግ በርካታ የስዕል ስራዎች የሚቀርቡ ሲሆን የተለያዩ ጉዳዮችን እንደሚዳስሱም ተገልጿል፡፡
አውደ ርዕዩ እስከ ፌቡራሪ 23 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ለጐብኚዎች ክፍት ሆኖ እንደሚቆይም አዘጋጁ ጐሹ አርት ጋለሪ ከላከው መግለጫ ለማወቅ ተችሏል፡፡