Saturday, 07 February 2015 12:52

አሜሪካ በተወሰኑ የኢትዮጵያአካባቢዎች የጣለችውንየበረራ እገዳ አነሳች

Written by 
Rate this item
(4 votes)

እገዳው ለ15 አመታት ተግባራዊ ሆኖ ቆይቷል
    የአሜሪካ ፌዴራል አቪየሽን ባለስልጣን የአገሪቱ አውሮፕላኖች በተወሰኑ የኢትዮጵያ የድንበር ካባቢዎች የአየር ክልል ውስጥ እንዳይበሩ የጣለችውንና ለ15 አመታት ተግባራዊ ሆኖ የቆየውን እገዳ ማንሳቱን አስታወቀ፡፡ባለስልጣኑ የበረራ እገዳውን የጣለው የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት በተቀሰቀሰበት ወቅት እንደነበር
አስታውሶ፣ እገዳው በተጣለባቸው አካባቢዎች የደህንነትና የጸጥታ ሁኔታ እየተሻሻለ መምጣቱንና የአደጋ ስጋት የሌለበት መሆኑን በጥናት በማረጋገጡ እገዳውን ማንሳቱን ባለፈው ረቡዕ ይፋ ባደረገው መረጃ አስታውቋል፡፡በወቅቱ በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የተከሰተውን የድንበር ግጭት በድርድር ለመፍታት የተጀመረው ጥረት መስተጓጎሉን ተከትሎ፣ በአካባቢው የነበረው አጠቃላይ ሁኔታ ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው በሚል የበረራ እገዳው እ.ኤ.አ በ2000 ግንቦት ወር መጣሉን የጠቀሰው የባለስልጣኑ መረጃ፣ እገዳው መነሳቱ በሚመለከታቸው የመንግስት አካላት መጽደቁን ተከትሎ፣ የአሜሪካ አውሮፕላኖች በየትኛውም የኢትዮጵያ የአየር ክልል ውስጥ መንቀሳቀስ እንደሚችሉ አስታውቋል፡፡

Read 2897 times