አርቲስት በስሟ 35 የፋሽንና የኮስሞቲክ ምርት መሸጫ ሱቆቿ ያሏት ሲሆን ከ12 በላይ የፋሽን ምርቶችና ከ14 ዓይነት በላይ ሽቶዎችን በመነገድ ገበያው እንደደራላት ተዘግቧል፡፡ በሪያሊቲ ቴሌቪዥን ተከታታይ ፊልሞች በመሳተፍ፤ በትላልቅ ፊልሞች በተጋባዥ ተዋናይነት በመስራት በስሟ በምታንቀሳቅሳቸው የፋሽንና የኮስሞቲክስ አምራችና አቅራቢ ኩባንያዎቿ ስኬታማ እንደሆነች የገለፀው “ኮንታክት ሚውዚክ”፤ ዘንድሮ የአባቷ የነበሩ ዓለም አቀፍ የሂልተን ሆቴሎችን ህጋዊ ወራሽነት መብት እንዳገኘች አመልክቷል፡፡