Saturday, 07 February 2015 13:56

አሜሪካ በጨረቃ ላይ ቁጥጥር ማድረግ ልትጀምር ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

*ውሳኔው ጨረቃ የማን ናት
በሚለው ጥያቄ ላይ ተጽዕኖ አለው ተብሏል

የአሜሪካ መንግስት፤ አገራት፣ የግል የህዋ ምርምር ተቋማትና ኩባንያዎች በጨረቃ ላይ የሚያከናውኗቸውን የንግድ ስራዎች በተመለከተ ቁጥጥር ማድረግ ሊጀምር እንደሆነ ዘ ኢንዲፔንደንት ዘገበ፡፡
አሜሪካ ቁጥጥር ማድረግ እንደምትጀምር ማስታወቋ፣ ጨረቃ የማን ናት፣ የተለያዩ ቁሳቁሶችን ወደ ጨረቃ መላክ የሚችሉትስ እነማን ናቸው የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ የተጀመሩ ጥረቶችን አንድ እርምጃ ያራመደ ነው ተብሏል፡፡
የአገሪቱን ኩባንያዎች ጨምሮ በመስኩ የተሰማሩ የመላው አለም ኩባንያዎች መንኮራኩሮችን ወደ ጨረቃ መላክና የተለያዩ ስራዎችን ማከናወን የሚችሉት ከአሜሪካ ፈቃድ ሲያገኙ ብቻ ነው ያለው ዘገባው፤ ፍቃዱን የሚሰጠውም የአገሪቱ የፌዴራል አቪየሽን ባለስልጣን እንደሚሆን ጠቁሟል፡፡
ባለስልጣኑ ያወጣው የቁጥጥር መመሪያ ኩባንያዎችና ተቋማት ወደ ጨረቃ ለሚያደርጉት ጉዞ ፈቃድ ከመስጠት በተጨማሪ፣ በጨረቃ ላይ የሚኖራቸውን ክልል የሚወስን ነው፡፡
አሜሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸደቀውንና ጨረቃ እና ሌሎች የህዋው አለም ቦታዎች በማንኛውም መንግስት ባለቤትነት ስር አይሆኑም የሚለውን ህግ እንደተቀበለች ያስታወሰው ዘገባው፣ ህጉ የግል ኩባንያዎች በጨረቃ ላይ እንዳያስቀምጡ ባይከለክልም፣ አሜሪካ ግን ይሄን አካሄድ ለመቆጣጠር መነሳቷን አስረድቷል፡፡

Read 2153 times