Saturday, 21 February 2015 13:59

“ቢግ ብራዘር” በማርስ ሊዘጋጅ ነው

Written by 
Rate this item
(2 votes)

*200ሺ ሰዎች አመልክተው 100 ለመጨረሻው ዙር አልፈዋል
*4 ሴቶችና 1 ወንድ በማርስ የሪያሊቲ ሾው ፕሮግራም ይሳተፋሉ

ኤድሞል በተባለው ኩባንያ የሚዘጋጀውና አምስት ተፎካካሪዎችን የሚያካትተው የ2024  የቢግ ብራዘር የቴሌቪዥን ሪያሊቲ ሾው ፕሮግራም በማርስ ፕላኔት ላይ ሊዘጋጅ ነው፡፡
ኩባንያው በድረገጹ ላይ ባወጣው  መረጃ እንደጠቆመው ፣ ማርስ ዋን በተሰኘው ፕሮጀክት አማካይነት ከ9 አመታት በኋላ ወደ ማርስ  ሊደረግ የታቀደው ጉዞ አካል በሆነው የቢግ ብራዘር ላይ ለመሳተፍ 200 ሺህ ሰዎች ያመለከቱ ሲሆን  ለመጨረሻው ዙር ያለፉት 100 ሰዎች ተለይተዋል፡፡
ከ100ዎቹ እጩ ተፎካካሪዎች መካከል 39 አሜሪካውያን፣ 31 አውሮፓውያን፣ 16 እስያውያን፣ 7 አፍሪካውያን እና 7 አውስትራሊያውያን እንደሆኑ ታውቋል፡፡ በማርስ ላይ በሚከናወነው የ2024 የቢግ ብራዘር ሾው ላይ የሚሳተፉት አራት ሴት እና አንድ ወንድ ተፎካካሪዎች እንደሚሆኑ የተገለጸ ሲሆን  ጉዞው 3.6 ቢሊዮን ፓውንድ እንደሚፈጅ  ታውቋል፡፡ በማርስ ላይ የሚከናወነው ቢግ ብራዘር  በየሁለት አመቱ እንደሚዘጋጅ የጠቆመው መረጃው፣ ወደ ማርስ የሚደረገው ጉዞ 200 ቀናትን ያህል እንደሚፈጅም አስታውቋል፡፡

Read 2712 times