Monday, 02 March 2015 10:34

ፖፑሌሽን ሚዲያ ሴንተር ሦስት መጻህፍት ያስመርቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

በፖፕሌሽን ሚዲያ ሴንተር አሳታሚነት የታተመውና በህፃናት ጉልበት ብዝበዛ ላይ ያተኮረው “ታጋቾቹ” የተሰኘ የአጫጭር እውነተኛ ታሪኮች መድበል እንዲሁም ቀደም ሲል ድርጅቱ ካሳተማቸው መጻህፍት  ተመርጠው ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎሙት “Blood Price” እና “Ditached in the Jungle” የሚሉ መጻህፍት የፊታችን ሐሙስ በሐርመኒ ሆቴል  ይመረቃሉ፡፡
መጻህፍቱ ከወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያና ከሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በትብብር እንደተዘጋጁ  ታውቋል፡፡ በምርቃትሥነ ስርዓቱ ላይ የመንግስት ባለስልጣናት፣የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ የፕሮግራሙ አዘጋጆች አስታውቀዋል፡፡ 

Read 1325 times