የሰዓሊ ቴዎድሮስ መስፍን (ቴዲ ማን) ከ30 በላይ የካርቱን ስዕሎች የቀረቡበት “ስዕላዊ ምፀት እና ስዕላዊ ስላቅ” የተሰኘ የስዕል ትርዒት ጥር 22 ቀን 2007 ዓ.ም በጋለሪያ ቶሞካ መከፈቱ የሚታወስ ሲሆን በነገው ዕለት ከረፋዱ 4፡00 ጀምሮ በሥራዎቹ ላይ ውይይት ይካሄዳል፡፡
የጋለሪው አርት ዳይሬክተር ሰዓሊ እሸቱ ጥሩነህን ጨምሮ ሌሎች ሰዓሊያን፣ የስዕል አፍቃሪያን፣ ጋዜጠኞችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በውይይቱ ላይ እንደሚሳተፉ የጋለሪው ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ነብዩ ግርማ ተናግሯል፡፡ ውይይቱ በሰዓሊው ስራዎች፣ በአሳሳል ፍልስፍናው፣ ስዕሎቹ ለአገራችን ስነ-ጥበብ ባላቸው ፋይዳና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥን ይሆናል ተብሏል፡፡ ጋለሪያ ቶሞካ 14ኛውን የስዕል ትርዒት ከአንድ ወር በኋላ ለመክፈት በዝግጅት ላይ እንደሆነም ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና