Monday, 02 March 2015 10:35

በሰዓሊ ቴዎድሮስ መስፍን የካርቱን ስዕሎች ላይ ውይይት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሰዓሊ ቴዎድሮስ መስፍን (ቴዲ ማን) ከ30 በላይ የካርቱን ስዕሎች የቀረቡበት “ስዕላዊ ምፀት እና ስዕላዊ ስላቅ” የተሰኘ የስዕል ትርዒት ጥር 22 ቀን 2007 ዓ.ም በጋለሪያ ቶሞካ መከፈቱ የሚታወስ ሲሆን በነገው ዕለት ከረፋዱ 4፡00 ጀምሮ በሥራዎቹ ላይ ውይይት ይካሄዳል፡፡
የጋለሪው አርት ዳይሬክተር ሰዓሊ እሸቱ ጥሩነህን ጨምሮ ሌሎች ሰዓሊያን፣ የስዕል አፍቃሪያን፣ ጋዜጠኞችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በውይይቱ ላይ እንደሚሳተፉ የጋለሪው ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ነብዩ ግርማ ተናግሯል፡፡ ውይይቱ በሰዓሊው ስራዎች፣ በአሳሳል ፍልስፍናው፣ ስዕሎቹ ለአገራችን ስነ-ጥበብ ባላቸው ፋይዳና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥን ይሆናል ተብሏል፡፡ ጋለሪያ ቶሞካ 14ኛውን የስዕል ትርዒት ከአንድ ወር በኋላ ለመክፈት በዝግጅት ላይ እንደሆነም ታውቋል፡፡

Read 1816 times