Print this page
Monday, 02 March 2015 10:38

የ5ጂ ቴክኖሎጂ ተመራማሪዎች በታሪክ እጅግ ፈጣን የኢንተርኔት ግንኙነት አደረጉ

Written by 
Rate this item
(5 votes)

የ5ጂ ፍጥነት ከ4ጂ በ65ሺህ እጥፍ ይበልጣል
 - 100 ፊልሞችን በሶስት ሰከንድ ማውረድ ያስችላል

   የሱሬ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች በታሪክ እጅግ ፈጣኑ የተባለለትን የ5G (የአምስተኛው ትውልድ) የኢንተርኔት መረጃ ልውውጥ ቴክኖሎጂ በሙከራ ደረጃ ተግባራዊ ማድረጋቸውን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
በአሁኑ ሰዓት በጥቅም ላይ ከሚውሉት የመረጃ ልውውጦች ፍጥነት በብዙ ሺህዎች እጥፍ የላቀ ነው የተባለለት የ5ጂ ፈጠራ፣ በሰከንድ አንድ ቴራ ባይት መጠን ያለው መረጃ የማስተላለፍ አቅም ያለው ነው፡፡
የዩኒቨርሲቲው የ5ጂ ፈጠራ ማዕከል ሃላፊ፤ አዲሱ ቴክኖሎጂ ከሶስት አመታት በኋላ በይፋ ተጠናቅቆ ለህዝብ እይታ እንደሚበቃ የተናገሩ ሲሆን ምርምሩን የሚመራው ኦፍኮም የተባለ ኩባንያም፤ ፈጠራው እስከ 2020 ድረስ በእንግሊዝ ተጠቃሚዎች እጅ ይገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁሟል፡፡
የቴክኖሎጂው ፍጥነት እጅግ የላቀ እንደሆነ የጠቆመው ቢቢሲ፤ የአንድ ሙሉ ፊልም መቶ እጥፍ ያህል መረጃ ያለውን ፋይል በሶስት ሰከንድ ብቻ ማውረድ (ዳውንሎድ ማድረግ) እንደሚያስችል  አስረድቷል፡፡ የ5ጂ ፍጥነት፣ በአሁኑ ሰአት ጥቅም ላይ እየዋለ ከሚገኘው 4ጂ አንጻር ሲወዳደር ከ65 ሺህ እጥፍ በላይ እንደሚበልጥም አመልክቷል፡፡

Read 2067 times
Administrator

Latest from Administrator