- አልቃይዳ በዋይት ሃውስ ላይ ጥቃት የመፈጸም ዕቅድ ነበረው
ኦሳማ ቢላደን በህይወት በነበሩበት ጊዜ በምዕራባውያን አገራት የሽብር ጥቃቶችን ለመሰንዘር በተያዙ ዕቅዶች ዙሪያ ከአልቃይዳ መሪዎች ጋር የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች መገኘታቸውን ስካይ ኒውስ ዘገበ፡፡
ከአልቃይዳ ጋር በመተባበር በእንግሊዝ የሽብር ጥቃቶችን ለመሰንዘር አሲሯል በሚል ክስ የተመሰረተበትን አቢድ ናስር የተባለ ፓኪስታናዊ ተማሪ ጉዳይ በመመርመር ላይ የሚገኘው የኒው ዮርክ ፍርድ ቤት ባለፈው ረቡዕ በዋለው ችሎት፣ ቢላደን ከቡድኑ መሪዎች ጋር የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች ለመጀመሪያ ጊዜ በማስረጃነት ቀርበዋል፡፡ ደብዳቤዎቹ ቢላደን በሩስያ፣ በአሜሪካ፣ በእንግሊዝና በሌሎች የምእራቡ አለም አገራት ላይ የሽብር ጥቃቶችን ለመሰንዘር ዝግጅት ሲያደርጉ እንደነበር ያጋለጡ ሲሆን በአቦታባድ ተደብቀውበት በነበረው ግቢ ውስጥ በአሜሪካ ወታደሮች እስከተገደሉበት ጊዜ ድረስ በተለያዩ የአለም ክፍሎች ከሚኖሩ የቡድኑ የጥቃት መሪዎች ጋር የሽብር ሴራ መልዕክቶችን ይለዋወጡ እንደነበር ያረጋገጡ ናቸው ተብሏል፡፡ አልቃይዳ በዋይት ሃውስ ላይ የሽብር ጥቃት የመሰንዘር ትልቅ እቅድ እንደነበረው የሚገልጽ ደብዳቤ ከመገኘቱ በተጨማሪ፣ ቢላደን አዳዲስ የጥቃት መፈጸሚያ መንገዶችን መቀየስ እንደሚገባ ከጥቃት መሪዎቹ ጋር ያደረጉትን ውይይት የሚጠቁሙ ደብዳቤዎችም ተገኝተዋል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ