Monday, 16 March 2015 10:11

ፎርብስ የአመቱን የዓለማችን 500 ቢሊየነሮች ይፋ አደረገ

Written by 
Rate this item
(12 votes)

- ቢል ጌትስ ለ16ኛ ጊዜ መሪነቱን ይዘዋል
- ቻይና በአንድ አመት 71 አዳዲስ ቢሊየነሮችን አፍርታለች
   በየአመቱ የዓለማችንን ቀዳሚ ቢሊየነሮች ዝርዝር የሚያወጣው ታዋቂው ፎርብስ መጽሄት ባሳለፍነው ሳምንት የ2015ን ምርጥ 500 የዓለማችን ቢሊየነሮችን ይፋ አድርጓል፡፡
ፎርብስ ለ29ኛ ጊዜ ይፋ ያደረገውን የዘንድሮ የዓለማችን ቢሊየነሮች ዝርዝር በቀዳሚነት የመሩት አሜሪካዊው የማይክሮ ሶፍት ኩባንያ መስራች ቢል ጌትስ ሲሆኑ፣ አጠቃላይ የሃብት መጠናቸውም 79.2 ቢሊዮን ዶላር ነው ተብሏል፡፡
ባለፈው አመት በነበራቸው ሃብት ላይ የ3 ቢሊዮን ዶላር ጭማሪ በማሳየት ለ16ኛ ጊዜ የዓለማችን ቁንጮ ባለጸጋ መሆናቸውን ያረጋገጡትን ቢል ጌትስ፣ በአመቱ 1.5 ቢሊዮን ዶላር ለበጎ ምግባር በስጦታ መልክ ቢለግሱም፣ ልግስናቸው አተረፈላቸው እንጂ አልቀነሰባቸውም፡፡
እሳቸውን ተከትለው የሁለተኛነትን ደረጃ የያዙት ደግሞ፣ 77.1 ቢሊዮን ዶላር ሃብት ያላቸው ሜክሲኳዊው የቴሌኮም ዘርፍ ባለጸጋ ካርሎስ ስሊም ሄሉ ናቸው፡፡
ሌላኛው ስመጥር አሜሪካዊ ባለሃብት ዋረን ቡፌት በ72.7 ቢሊዮን ዶላር ሃብት የአመቱ የዓለማችን ሶስተኛ ባለጸጋ ተብለዋል፡፡
አመቱ በአለማችን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ቢሊየነሮች የታዩበት እንደሆነ በሚያሳየው የዘንድሮው የፎርብስ ዝርዝር ውስጥ፣ እስከ 500ኛ ደረጃ የያዙ በድምሩ 1826 ቢሊየነሮች የተካተቱ ሲሆን፣ አለማችን ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ብቻ 181 ቢሊየነሮችን አግኝታለች፡፡

Read 4966 times