Monday, 06 April 2015 09:24

የስዊድን ፓርላማ “ህገ-ወጥ ዳንስ”ን ከለከለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

- የማስደነስ ፈቃድ የሌላቸው ባሮችና የምሽት ክበቦች ይቀጣሉ
- ፖሊስ ዳንስ ለግርግርና ለብጥብጥ ይዳርጋል ብሏል
- 10 ሺህ ዜጎች የሚሳተፉበት የጎዳና ላይ የዳንስ ተቃውሞ ይደረጋል
   የአገሪቱ ዜጎች ህዝብ በተሰበሰበባቸውና በመዝናኛ ስፍራዎች የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በተመለከተ ገደብ የሚጥል አዋጅ አውጥቶ ሲተገብር የቆየው የስዊድን ፓርላማ፣ የአዋጁ አንድ አካል የሆነውና ህገ-ወጥ ዳንስን የሚከለክለውን አነጋጋሪ ህግ ተግባራዊ መደረጉን እንዲቀጥል መወሰኑን ዴይሊ ሜል ዘገበ፡፡
የአገሪቱ ፖሊስም ህገወጥ ዳንስ፤ለግርግርና ብጥብጥ የሚዳርግ በመሆኑ ህጉን እንደሚደግፈው ያስታወቀ ሲሆን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው፤ አሳፋሪ የቢሮክራሲ መገለጫ በመሆኑ ሊሻር ይገባል ሲሉ ነቅፈውታል፡፡ ፓርላማው ድምጽ የሰጠበትና እንዲቀጥል የወሰነበት ይህ ህግ፣ ሙዚቃ ስለሰሙ ብቻ እግራቸውን ለዳንስ የሚያነሱ ግለሰቦችን በህገወጥነት የሚፈርጅ ሲሆን፣ የማስደነስ ፍቃድ የሌላቸው የባርና የምሽት ክለብ ባለቤቶች ሲያስደንሱ ከተገኙ እንደሚቀጡ ይደነግጋል፡፡
ደንበኞቻቸው በሰሙት ሙዚቃ ሁሉ ሳያቋርጡ ሲደንሱ ወይም ፈቃድ ሳያገኙ ሲውረገረጉ ከተገኙም የባርና የምሽት ክለብ ባለቤቶች እንደሚቀጡ ህጉ ይገልጻል፡፡ ህጉን የተቃወሙት አንድሪያስ ቫርቬስ የተባሉ ስዊድናዊ የምሽት ክለብ ባለቤት፣ ከዚህ በፊት እንደተደረገው ሁሉ በመጪው ነሐሴ ወር ላይ ህጉን የሚቃወም የጎዳና ላይ የዳንስ ተቃውሞ ለማድረግ  ማቀዳቸውን ተናግረዋል፡፡ በጎዳና ላይ ዳንሱ ከ10 ሺ በላይ ሰዎች ይሳተፋሉ ብለው እንደሚገምቱም ገልጸዋል፡፡

Read 2292 times