Tuesday, 14 April 2015 07:40

ጅቡቲ በየመን ሁቲዎች የተከማቸ ከባድ መሳሪያ እንዲወገድላት ጠየቀች

Written by 
Rate this item
(4 votes)

     የየመን ሁቲዎች በባብኤል መንደብ በሚገኙ ደሴቶች ላይ ያከማቹት ከባድ የጦር መሳሪያ በአለምአቀፉ የመርከብ እንቅስቃሴ ላይ ስጋት እንደጋረጠ የጠቆመችው ጅቡቲ፤ በሳዑዲ አረቢያ የሚመራውና የመን ላይ ወታደራዊ እርምጃ በመውሰድ ላይ የሚገኘው ጥምር ሀይል እንዲያስወግደው ጠየቀች፡፡
በአለም አቀፍ ደረጃ ብዙ የባህር ላይ እንቅስቃሴዎችን በማስተናገድ የሚታወቀው የቀይባህር የፀጥታና ደህንነት ሁኔታ በየመኑ ሁቲ አማፂያን ምክንያት ስጋት እንደተጋረጠበት መረጃዎች ይጠቁማሉ። ኢትዮጵያ በብቸኝነት የምትጠቀምበት ወደብ ባለቤት የሆነችው ጅቡቲ፤ የሁቲዎቹ እንቅስቃሴ በአለም አቀፉ የመርከቦች ደህንነት ላይ ስጋት መደቀኑን አስታውቃለች፡
የጅቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሀሙድ አሊ ዩሱፍ ሰሞኑን በሰጡት መግለጫ፤ አገራቸው ጥምር ሀይሉን እንደምትደግፍ ጠቁመው በባብኤል መንደብ ሰርጥ  ባሉ ደሴቶች ላይ በሁቲዎች የተከማቸው ከባድ የጦር መሳሪያ ለአለም አቀፍ የመርከቦች ዝውውር ስጋት በመሆኑ በጥምር ሀይሉ እንዲወገድ ጠይቀዋል፡፡
 በቀይባህር በኩል የተፈጠረው የፀጥታና የደህንነት ስጋት በኢትዮጵያ መርከቦች ጉዞ ላይ የፈጠረውን ሁኔታ በተመለከተ ለማጣራት ያደረግነው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

Read 2103 times