Tuesday, 14 April 2015 07:48

የ129 ሺህ ዶላር የአልማዝ ቀለበቶችን ለባለቤቶቹ የመለሰችው ኢትዮጵያዊት ተሸለመች

Written by 
Rate this item
(10 votes)

 ከዚህ በፊትም መታጠቢያ ክፍል ውስጥ ያገኘችውን የአልማዝ ቀለበት ለባለቤቱ መልሳለች
-በኳታር በመታጠቢያ ቤት ውስጥ ያገኘቻቸውን 129 ሺህ ዶላር የሚያወጡ ሁለት የአልማዝ የጣት ቀለበቶች ለባለቤቶቹ ያስረከበችው ኢትዮጵያዊት የጽዳት ሰራተኛ፣ ላሳየችው ታማኝነት በአሰሪዎቿ መሸለሟን ዶሃ ኒውስ ዘገበ፡፡
አንድነት ዘለቀው የተባለችው የ32 አመት ኢትዮጵያዊት የጽዳት ሰራተኛ፣ በምትሰራበት የኳታር ብሄራዊ የስብሰባ ማዕከል መታጠቢያ ክፍል ውስጥ ተረስተው ላለፉት አራት አመታት በማዕከሉ በጽዳት ሰራተኛነት ተቀጥራ ስትሰራ ለቆየችው አንድነት የገንዘብ ስጦታውን ያበረከቱት የማዕከሉ ዋና ስራ አስኪጅ ኬን ጄሚሰን፣ ግለሰቧ ያሳየችው የታማኝነት ተግባር እንደሚያስመሰግናትና ለማዕከሉም ኩራት እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
ቀለበቶቹን ባገኘችበት ቅጽበት፣ ይሄኔ የቀለበቶቹ ባለቤት እንደጠፋት ስታውቅ ምን ይሰማት ይሆን የሚል ስሜት እንደተሰማትና ባአፋጣኝ ለማዕከሉ ረዳት ስራ አስኪያጅ ደውላ ስለጉዳዩ በመንገር ቀለበቶቹን እንደመለሰች አንድነት ለዶሃ ኒውስ ተናግራለች፡፡ ታማኝነት ታላቁ የህይወት መርህ እንደሆነ አምናለሁ ስትልም ተናግራለች፡፡ አንድነት ከዚህ በፊትም አል ሙክታር በተባለ የኳታር የጽዳት ኩባንያ ውስጥ ተቀጥራ በምትሰራ ወቅት ውድ ዋጋ የሚያወጣ ከአልማዝ የተሰራ የጣት ቀለበት በመታጠቢያ ክፍል ውስጥ ወድቆ አግኝታ ለባለቤቶቹ ማስረከቧን ዘገባው አስታውሷል፡፡
የጣት ቀለበቶቹ ባለፈው የካቲት ወር በማዕከሉ በተካሄደው የዶሃ የጌጣጌጦችና የእጅ ሰዓቶች ኤግዚቢሽን ላይ የጠፉ እንደነበሩ ያስታወሰው ዘገባው፤ ማእከሉ ለኢትዮጵዊቷ የሸለመው ገንዘብ ምን ያህል እንደሆነ አለመገለፁን ጠቁሟል፡፡

Read 4296 times