Monday, 20 April 2015 14:06

“ፍቱን” መጽሔት ከህትመት ታገደች

Written by 
Rate this item
(4 votes)

በማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ በየሳምንቱ ቅዳሜ ለንባብ የምትበቃው “ፍቱን” መጽሄት ከህትመት ታገደች፡፡ በአገሪቱ የሚገኙ የግልም ሆነ የመንግስት ማተሚያ ቤቶች መፅሔቷን እንዳያትሙ ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡
የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ባስተላለፈው መልዕክት የመፅሄቷን አሳታሚ አቶ ፍቃዱ በርታን ለጥያቄ ቢፈልጓቸውም ሊያገኟቸው አለመቻላቸውን ጠቁሟል፡፡ አሳታሚዎቹ፤ ከመንግስት ደረሰኞች ጋር ተመሳሳይ የሆኑ ደረሰኞችን በማሳተም ህገወጥ ስራ ሲሰሩ ተደርሶባቸዋል ያለው የባለስልጣኑ መግለጫ፤ በዚህ ምክንያትም መፅሄቷ ከህትመት ውጪ እንድትሆን ለማድረግ የሚያስችል የፍርድ ቤት ማገጃ ማውጣታቸውንና የትኛውም ማተሚያ ቤት መፅሄቷን ከማተም እንዲቆጠብ አሳስበዋል፡፡
“ፍቱን” መፅሄት በማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ አተኩራ በየሳምንቱ ቅዳሜ ለንባብ የምትበቃ መፅሔት ነበረች፡፡

Read 1780 times