Saturday, 02 May 2015 11:45

የግጥም ጥግ

Written by 
Rate this item
(11 votes)

አ ቤት!
ኤሎሄ  ቅኝቱ  ጠፍቶኝ
የነገለ በገና አቅፌ
በጉልበቴ ተቀምጬ፤
በፍታቴ እስክስታ ብወርድ
እዝል አራራዩን ባላዝነው
ቅኔ ማህሌቱን  ገልብጬ፤
የሀሩር በረሀ አበባው
ዋግ እንዳጠናፈረው እሸት
እማሳው መሀል ብገተር፤
አለቅጥ ጠግበው በሚያናፉ
ዝሆኖች መሀል እንደ ድርጭት
አቅሌን ስቼ እምውተረተር፤
ፈተና ያቆመኝ ሀውልት
አልሟሟም ያልኩ ቢመስል
ባያነባ ሙጭሙጭ አይኔ፤
እምነቴ ቢያጠጥረኝ ነው
ምናቤ የረገጠው እርካብ
ቢያዝለኝ ጣራ ውጥኔ፡፡
እንደ ምኞታችንማ ጉስቁልና
እንደ ሚዛናችን መራቆት
እንደ ነፍሳችን ግልቢያ መጃጀት፤
መርዷችን ባይሰማ እንጂ
ወገን ከሌለንማ ቆየን
እንደ ሩቁ ተስፋችን መዘግየት፡፡
አቤት!    አቤት!!    አቤት!!!
/ፈለቀ አበበ፤ 1989 ዓ.ም -
ተረት ሰፈር/

Read 3936 times