Saturday, 02 May 2015 12:42

የቱሪስት መረጃ ገበያ ላይ ዋለ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(1 Vote)

      በበረከት ማቱሳላና በሰማኸኝ ደሳለኝ በእንግሊዝኛ ቋንቋ “Exodus South Ethiopia Travel Guide Book” በሚል ርዕስ ተፅፎ በኤክሰደስ ፕሮሞሽን ማስታወቂያ ስራ ድርጅት አሳታሚነት የታተመው የጉብኝትና የጉዞ መመሪያ መፅሀፍ ሰሞኑን ገበያ ላይ ዋለ፡፡ መፅሀፉ በተለይም በደቡብ ኢትዮጵያ የሚገኙ ታሪካዊ፣ ተፈጥሮአዊ፣ ባህላዊና ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስህቦችን፣ ከ30 በላይ ከተሞችን፣ የባሌ ተራራን ጨምሮ 12 ብሄራዊ ፓርኮችን የሚያስቃኝ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ለቱሪስቶች ጠቃሚ የሆኑ የጉዞ ምክሮችን እንዳካተተም ለማወቅ ተችሏል፡፡ 202 ገጾች ያለው በየሃገሩ የሚገኙ የማፊያና የአገልግሎት ሰጪ ድርጅቶችን እንዲሁም በአደጋ ጊዜ ተጠሪ የሆኑ ተቋማትን የስልክ አድራሻ አካቶና የተሰናዳ የቱሪስት መረጃ መፅሀፍ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ መፅሀፉ በ17 ዶላር፣ በ15 ዩሮ እና በ14 ፓውንድ ለገበያ መቅረቡም ተገልጿል፡፡

Read 1571 times