Sunday, 10 May 2015 15:24

ሚዩዚክ ሜይዴይ ያቋረጠውን የመፃሕፍት ውይይት ጀመረ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ የመፃሕፍት ንባብ እና ውይይት ፕሮግራም በነገው ዕለት “ዘ ማሳካር ኦፍ ደብረ ሊባኖስ ኢትዮጵያ 1937” በተሰኘው የደራሲ ኢያን ካምፔል መጽሐፍ ላይ በነገው ዕለት በብሔራዊ ቤተመፃሕፍትና ቤተመዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ውይይት ያካሂዳል፡፡
ለውይይቱ መነሻ ሃሳብ የሚያቀርቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምሕር የሆኑት ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ሲሆኑ የሥነ ፅሁፍ ቤተሰቦች በዚህ ውይይት ላይ እንዲታደሙ ሚዩዚክ ሜይዴይ ጋብዟል፡፡
ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ለ6 ወራት ያህል በየ15 ቀኑ የሚያደርገውን የመፃህፍት ውይይት አቋርጦ እንደነበር ይታወሳል፡፡

Read 1689 times