Saturday, 16 May 2015 10:10

ሃና ላላንጐን ደፍረው ለሞት ዳርገዋል የተባሉት ጥፋተኛ ተባሉ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(2 votes)

የ16 አመቷን ታዳጊ ሃና ላላንጐን አስገድደው በመድፈር ለሞት አብቅተዋታል የተባሉት 5 ግለሰቦችን ፍ/ቤት ትናንት ጥፋተኛ ብሏቸዋል፡፡
የ10ኛ ክፍል ተማሪ የነበረችውን ታዳጊ ለ5 ቀናት አግተው በመያዝ እየተፈራረቁ መድፈራቸውን ፍ/ቤቱ በማስረጃ አረጋግጦ ጥፋተኛ ያላቸው 1ኛ የታክሲ ሹፌር:- ሳምሶን ስለሺ፣ በዛብህ ገ/ማርያም፣ በቃሉ ገብረ መድህንና የታክሲ ረዳቶቹ ኤፍሬም አየለና ተመስገን ፀጋዬ ናቸው፡፡
ተከሳሾቹ፤ ዕድሜያቸው ከ18 አመት በታች የሆነ ታዳጊን በመድፈርና በከባድ የሰው መግደል ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው የነበረ ሲሆን የግራ ቀኙን ክርክር በዝግ ችሎት ሲመለከት የቆየው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 3ኛ የወንጀል ችሎት በሁሉም ተከሳሾች ላይ የጥፋተኝነት ብይን ሰጥቷል፡፡
የመጨረሻ የቅጣት ውሣኔ ለመስጠትም ፍ/ቤቱ ጉዳዩን ለግንቦት 14 ቀጥሯል፡፡  

Read 1864 times