Print this page
Saturday, 13 June 2015 15:17

ኒውዮርክ ያመለጡ እስረኞችን ለጠቆመ 100 ሺህ ዶላር ትሰጣለች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 - በእስር ቤቱ የ150 አመት ታሪክ ሲያመልጡ የመጀመሪያዎቹ ናቸው
  - ድንበር አቋርጠው ወደ ካናዳ ሳይገቡ አልቀሩም ተብሏል
     የኒውዮርክ አገረ ገዢ አንድሪው ኮሞ ባለፈው አርብ ሌሊት ዳኔሞራ በተባለችው ከተማ ከሚገኝ እስር ቤት ያመለጡትን ሁለት ነፍሰ ገዳዮች በተመለከተ መረጃ ለሰጣት ሰው፣ ግዛቲቱ 100 ሺህ ዶላር ወሮታ እንደምትከፍል ማስታወቃቸውን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
ሪቻርድ ማት እና ዴቪድ ስዊት የተባሉት እነዚህ አደገኛ ነፍሰ ገዳዮች ከፍተኛ ጥበቃ በሚደረግለት በዚህ እስር ቤት የ150 አመታት ታሪክ አምልጠው መጥፋት የቻሉ የመጀመሪያዎቹ ታራሚዎች ናቸው ያለው ዘገባው፤የታሰሩበትን ክፍል የብረት ግድግዳ በመቁረጥ በፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች ውስጥ ለውስጥ ሾልከው እንዳመለጡ ገልጧል፡፡
“እነዚህ ነፍሰ በላዎች አሁንም የከፋ ወንጀል ከመፈጸም ወደኋላ የማይሉ ናቸው” ብለዋል፤አገረ ገዢው አንድሪው ኮሞ፣ ምናልባትም እስረኞቹ ድንበር አቋርጠው ወደ ካናዳ ሳይገቡ እንዳልቀሩ ግምታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ሁለቱ እስረኞች ማምለጣቸውን ተከትሎ፣ ፖሊስ በአካባቢው የሚገኙ ጎዳናዎችን ዝግ አድርጎ ጉዳዩን በጥብቅ መመርመሩንና  በግዛቲቱ የሚደረገው የደህንነት ፍተሻና ፍለጋ በከፍተኛ ሁኔታ ተጧጡፎ መቀጠሉን የገለጸው ዘገባው፣ ከ200 በላይ ፖሊሶችም በአነፍናፊ ውሾችና በአየር ላይ አሰሳ በታገዘ እስረኞቹን የማደን ስራ መጠመዳቸውን አስረድቷል፡፡
ሪቻርድ ማት አንድን ግለሰብ በማገትና በመግደል ወንጀል ተከሶ የ25 አመታት የእስር ቅጣት ላይ እንደነበርና፣ ዴቪድ ስዊትም አንድን የፖሊስ ሃላፊ በመግደሉ የእድሜ ልክ እስር ፍርደኛ እንደነበር ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1139 times
Administrator

Latest from Administrator