Saturday, 20 June 2015 11:28

የድረ-ገጾች ፍጥነት በአለማቀፍ ደረጃ ቀንሷል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  በድረ-ገጾች ላይ የሚጫነው መረጃ መጠን ከሶስት አመታት በፊት ከነበረው በእጥፍ ያህል መጨመሩን ተከትሎ፣ የድረ-ገጾች ፍጥነት በአለማቀፍ ደረጃ መቀነሱንና ድረ-ገጾችን ለመክፈት የሚፈጀው አማካይ ጊዜ መጨመሩን ሲኤን ኤን ዘገበ፡፡
በአሁኑ ወቅት አንድ ድረ-ገጽ ሳይት የሚይዘው አማካይ የመረጃ መጠን 2.1 ሜጋ ባይት ደርሷል ያለው ኤችቲቲፒ፣ ለድረ-ገጾች ፍጥነት መቀነስ በምክንያትነት ከተጠቀሱት መካከል ቪዲዮዎች፣ ስዕሎችና ድህንነትን ለማስጠበቅ በሚል የሚጫኑ ሌሎች መረጃዎች መብዛታቸውና የመረጃ ዝውውሮች መጨናነቃቸው ይገኙበታል፡፡
ስማርት ፎኖችና ታብሌቶች በስፋት ለኢንተርኔት አገልግሎት መዋላቸውም ለድረ-ገጾች ፍጥነት መቀነስ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ዘገባው ጠቁሞ፣ ምንም እንኳን ፍጥነቱ የቀነሰው በሰከንዶች እድሜ ቢሆንም፣ እያንዳንዷ ማይክሮ ሰከንድ ትልቅ ዋጋ በያዘችበት በዚህ የመረጃና የፈጣን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ዘመን ጉዳዩ አሳሳቢ ነው የሚል አስተያየት መሰጠቱን አስታውቋል፡፡
የኢንተርኔት ተጠቃሚነት በአለማቀፍ ደረጃ እያደገ መምጣቱን ተከትሎ የኔትወርክ መጨናነቅ መፈጠሩ፣ የብራውዘሮች አይነትና አቅም መለያየትም ለችግሩ መከሰት በምክንያትነት ተጠቅሰዋል፡፡

Read 1245 times