Saturday, 27 June 2015 10:15

“ፔንታገን” በአለማችን በሰራተኞች ብዛት መሪነቱን ይዟል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 በያዝነው የፈረንጆች አመት በርካታ ሰራተኞችን ቀጥረው እያሰሩ ከሚገኙ የዓለማችን ተቋማትና ድርጅቶች መካከል፣ 3.2 ሚሊዮን ሰራተኞችን የሚያስተዳድረው የአሜሪካ መከላከያ ሚንስቴር ፔንታገን በሠራተኞች ብዛት መሪነቱን መያዙን ፎርብስ መጽሄት ዘገበ፡፡
የአለም የኢኮኖሚ ፎረም ሰሞኑን ይፋ ያደረገውን የጥናት ውጤት ጠቅሶ ፎርብስ ባለፈው ማክሰኞ እንዳስነበበው፣ የቻይና ህዝቦች የነጻነት ጦር 2.3 ሚሊዮን ሰራተኞችን በመያዝ በሁለተኝነት ሲከተል፣ ታዋቂው አለማቀፍ የሸቀጣሸቀጥ ሱፕርማርኬት  ዎልማርት በ2.1 ሚሊዮን ሰራተኞች ሶስተኛውን ደረጃ ይዟል፡፡ በአመቱ በርካታ ሰራተኞችን በስሩ ቀጥሮ በማስተዳደር ከአለማችን አራተኛውን ደረጃ የያዘው ደግሞ 1.9 ሚሊዮን ሰራተኞች ያሉት ታዋቂው የምግብ አምራች ኩባንያ ማክዶናልድ ነው፡፡
የእንግሊዝ ብሄራዊ የጤና አገልግሎት ድርጅት በ1፣7 ሚሊዮን ሰራተኞች አምስተኛ ደረጃን እንደያዘ የገለጸው ዘገባው፣ የቻይና ብሄራዊ የነዳጅ ኮርፖሬሽን በ1.6 ሚሊዮን፣ የቻይናው ስቴት ግሪድ ኮርፖሬሽን በ1.5 ሚሊዮን፣ የህንድ ምድር ባቡር ኩባንያ በ1.4 ሚሊዮን፣ የህንድ የጦር ሃይል በ1.3 ሚሊዮን እንዲሁም ሆን ሃይ ፕሪሲዥን የተባለው ኩባንያ በ1.2 ሚሊዮን ሰራተኞች እስከ አስረኛ ደረጃ ይዘዋል ብሏል፡፡

Read 2591 times